እኩልነት
ቀልቤ ሲነግረኝ እምቢ አልኩትና
መታረዝ መጠማቴን ችላ አልኩትና
እንደ ዲዮጋን ሰው ፍለጋ ወጣሁና. . .
ግራ ቀኝ ብዳክር ሳልቆርጥ ተስፋ
እንኳን ሰዉ እኔው ራሴ ለራሴ ጠፋ
ለካስ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ አገሩ በሞላ
ሳናውቀው ተሽጠን ኖሯል እንዳለን በጅምላ
ለመሸጤ እንደ ደረሰኝ የቆረጡልኝ
እያለሁ ላለመኖሬ ያረጋገጡልኝ
መሸጫ ዋጋዬን ነው መሰል
አንተም እኩል ነህ ነው ያሉኝ!
#ብሩክ ዶን ብሩኖ፣ አዲስ አበባ ሐምሌ 22፣
2008 ዓመተ ኢትዮጵያ
No comments:
Post a Comment