Tuesday, November 22, 2016

Unanswered Question



Unanswered Question
?

Mapped like a question Mark,
A question from dawn to dusk,
A question of imported hostility,
That quests our fraternity.

A question asked for alien bread
When at home better can be baked
A question to be given,
Of what is taken,
Oh! Africa what unanswered question!
                                                                                                1998 Addis Ababa University

Unanswered Question



Unanswered Question
?

Mapped like a question Mark,
A question from dawn to dusk,
A question of imported hostility,
That quests our fraternity.

A question asked for alien bread
When at home better can be baked
A question to be given,
Of what is taken,
Oh! Africa what unanswered question!
                                                                                                1998 Addis Ababa University

Friday, November 18, 2016

ይቅርታ



ይቅርታ

ሳናውቅ ላጠፋነው፣
አውቀንም ላጠፋነው፣
ካንደበት ለወጣው፣
ለተነፈስነው፣
ሰውን በኪሱ ለፈረጅነው፣
ዕድሜን በቁጭ ለፈጀነው፣
ጊዜን ገዝግዘን አስገዝግዘን
አላፊ ነው ብለን ለሰየምነው
ቆርጠን ቆራርጠን
ተቀራምተን
በጊዜ ላይ ላለመጥነው፣
በተኛንበት ነግቶ ለመሸብን
ምጽድቅ ለገነነብን፣
የኛነት ኅብር በመላ መላችን
በአካላችን ነግሦብን
ገንዘብ ሃይማኖት ሆኖን
በቀኖናው ለኖርነው
ስሜታችንን ላስገዛነው፣
በእርሱ አልፋና ኦሜጋነት
ስንት በር ተከፍቶ ስንቱ በር ተዘጋ
ያንዱ ክረምት የሌላው በጋ
ስንንሿከክ፣ ስናሿክክ
ስናላክክ፣
በዘመን ላይ ዘመን ሲተካ
አንድ ጭቃ አንድ ወሬ ስናቦካ
ቁምነገር ሳይመረግ . . .  ቤቱም ሳይመረግ፣
የቤታችን መሠረት በጅምር ተናጋ
ልፋታችን ሁሉ አጥቶ ዋጋ
ያቆምነው ዋልታው ዘሞ፣
ጊዜ ጥሎን ሲሄድ ገስግሶ
የኛን ዘመን ብሂል ጥሶ በጣጥሶ
ሕያውነታችን ባክኖ፣
በደኅንነታችን ለታየው ገኖ፣
እንደ አሮጌ ዕቃ የሚጣል የትም
እንደ ሸንኮራ ጊዜን ብንመጠውም
ብንመጠምጠውም
እሱ እኛን እንጂ እኛ እሱን አልጣልንም
የትም ለቀረነው . . .  ስማችንን ሜድ ላይ የጣልነው
ክብራችንን አፈር ያበላነው
ለሥራ መፍታታችን ዋስትና
ለስንፍናችን ዕውቅና
ከትብያ መጣን ወደ ትብያ
ብለን አንድ ላይ ለዘመርነው
አቦ ኃይሉ ጊዜ ይቅር በለን፣
በምህረትህ ደግመህ ጐብኘን
እያየህ ሥቀህ አትለፈን
ሰላም ለነፍሳችን
ለብኩን ሕይወታችን!
ጊዜ ኃይሉ ሰላሙን ስጠን!
በፀፀት አትደቁሰን!
በጨለማ እንደኖረን በጨለማው ውስጥ ተወን
ጊዜ ኃይሉ ባክህ ብርሃን አታሳየን
ራሳችን ጊዜ መሆናችንን አትንገርን።

እንደ ፈረንጆቹ 1997