Friday, March 30, 2018

መሲህ ይመጣል ገና

መሲህ ይመጣል ገና

የያዘ ይዞት ጥላውን ቢሸጠው
ጥላ አይሸጥም'ንጂ ዋለልኝ ማን አለው
የመብራት ልጅ ፋኖስ ማር ነሽ ያሏት
ኃይለመስቀል እንድትሆን ጌጥ ያረጓት
ማር እንደነበር ጌታቸው መች ያኔ ገባቸው
ቼ ብለው ፈረሱን ዘመን ማሰሳቸው
ዓይን ራሱን አለማየቱ መች ያኔ ገባቸው
አይሁድ አላመኑም የጌታን ልጅ አልሰቀሉም
አጭበርባሪውን እንጂ መሲሁን አልነኩም
መሲህ ይመጣል ገና፣ አልቆረጥንም ተስፋ
ሙሴ ይመራናል ሌት ተቀን ሳያንቀላፋ
እያዩ አላዩም ሰምተውም አልሰሙም
ሀብታም ድሀ ቤት በጭራሽ አይገባም


መታሰቢያነቱ ለሁሉም ድሀ ቤት ገብተው ለሞቱ ሀብታሞች

በዕለተ ዑራኤል መጋቢት 2018 (በቊጥር ሲቀለድ)



Tuesday, March 27, 2018

ምርጥ ሐበሻና የዜሮ (የክብ) ትስስርና ከአራት ማዕዘን ቅርጽ ጋ ያለው ነገር


ምርጥ ሐበሻና የዜሮ (የክብ) ትስስርና ከአራት ማዕዘን ቅርጽ ጋ ያለው ነገር

  1. እውነተኛ ሐበሻ ሲወለድም፣ ሲኖርም፣ ሲሞትም ጎጆ ቤት ውስጥ ነው፤ ጎጆ ቤት ቅርጹ ክብ ነው። ኮንዶሚኒየም ያለውን የኑሮና አኗኗር ስኬት እዚህ ላይ ልብ ይሏል። 
  2.  እንደ ተወለደ መሀል አናቱ ላይ ክብ ቅቤ ይደረጋል። በክብ ቅርጽ የተድቦለቦለ ቅቤ ይውጣል። ሁለቱም ዜር ቅርጽ አለው። 
  3.  ዐርባ ወይም ሰማንያ ቀን ሲሞላው ለክርስትናው በክብ ገንዳ ተጠምቆ በክብ እንጀራ ላይ ይንደባለላል።    
  4.  የሚበላው እንጀራ፣ ጢቢኛው፣ ቂጣው፣ ሙልሙሉ፣ አምባሻው፣ ቆጮው፣ ዳቦው የሚጋገረው የግድ በክብ ቅርጽ ነው።     
  5. ወጥ የሚወጣው በክብ ቅርጽ ያለው ጭልፋ ክብ ተሠርቶ ነው። ገንፎም የሚቀርበው በክብ ቅርጽ መሃሉ ላይ ክብ ጉድጓድ ተበጅቶ ቅቤ ፈሶበት ነው።    
  6.  ሐበሻ ሲያድግ ቁንጮ ተላጭቶ ነው። ቁንጮ ክብ ቅርጽ ነው። አሁንም ከዜሮ አልራቀም።    
  7.  ሐበሻ አንገቱ ላይ ክርስቲያን ከሆነ ማእተብ፣ ሲልም ጥምጣም ወይም ሙስሊም ከሆነ ቆብ አያጣውም።    
  8.  ቄስ ትምህርት ሲማር ዛፍ ሥር ክብ ሠርቶ ነው። ክብ ሆኖ የተማረው ዕድሜ ልክ እስከ ዕለተ ሞቱ የማይስተው በደንብ የሚገባው ትምህርት ነው። አራት ማዕዘን ክፍል ሆነ በአራት ማዕዘን ሠሌዳ ተምሮ ለውጥ ሲያመጣ አላየንም። ለምለሚቱ አገሬ እያለ ትላንትም ሲረዳ ነበር ዛሬም ይረዳል።   
  9.  አይሮፕላን ክብ ቅርጽ ስላለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም ውስጥ ካሉ ምርጥ አየር መንገዶች አንዱ ለመባል ቢችልም ያንኑ አይሮፕላን ያበረረ ድንቅ ሐበሻ አብራሪ መኪና ሲይዝ ሥርዓት ሲጥስ ወይም አደጋ ሲደርስበት ብሎም አደጋ ሲያደርስ ይታያል፤ ምክንያቱም መኪና ቅርጹ አራት ማዕዘን ነው። ሐበሻ የአራት ማዕዘን ነገር አለርጂክ ነው ብለናል።   
  10.  ቤተክርስቲያኑ መስጊዱ ሁሉ ክብ ቅርፅ ነው። አራት ማዕዘን ከሆነ መጤ ስለሆነ ችግር ፈጣሪ ነው።     
  11.  እንስራው፣ ድስቱ፣ ምንቸቱ፣ አገልግሉ፣ ጣሳው፣ ስኒው፣ ሽክናው፣ ማክዳው፣ የቤት ቁሳቁሱ ሁሉ ክብ ነው።    
  12.  አፈርሳታ፣ ዳኝነቱ፣ ጉባኤው የሚከናወነው ክብ ሠርቶ ተቀምጦ ፊት ለፊት እየተያየ ነው። በአራት ማዕዘን አቀማመጥ ውጤታማ መሆን አይቻልም።    
  13.  ክብ የማይሠሩ ነገሮች እንኳ ቢኖሩ የግድ በተራ መዞር አለባቸው። ለምሳሌ፦ ጽዋ፣ ጉዳይ ለማስፈጸም ቢሮ መሄድ፣ ማኅበር፣ ዕቁብ፣ ዕድር ወዘተ።  
  14.  ሐበሻ በአራት ማዕዘን ቅርጽ አንድ ነገር ከሠራ እጅግ የመረረ ቁምነገር ወይም አስፈሪ ጉዳይ ነው። ለምሳሌ፦ ክታብ፣ ሬሳ ሣጥን፣ መቃብርና የመቃብር ድንጋይ፣ ብራና መጽሐፍ፣ መስቀል ወዘተ።    
  15.  በአራት ማዕዘን ቅርጽ የሚዘጋጁት ነጠላ፣ ኩታ፣ ጋቢ፣ ጃኖ የክት ናቸው። ዝም ተብሎ አይለብሱም።   
  16.  የጥንት ባሕላዊ ሥዕሎች በሙሉ እንደሚያሳዩት ሰው ፊቱ ቅርጽ ክብ ነው። ሁሉ ነገሩ ክብ ነው። ወይም ለክብ የተጠጋ ነው።   
  17.  ክብ (ቀለበት) ያለበት ፊደል ሳይጠቀሙ ምንም የተሟላ ዓርፍተ ነገር በግዕዝ፣ በትግርኛ ሆነ በአማርኛ ወዘተ መጻፍ አይቻልም።   
  18.  አክሱም ሐውልት ጫፉ ክብ ነው። ላሊበላ የተፈለፈለው ክብ ቅርጽ ባለው መሬት ውስጥ ተከቦ ነው።   
  19.  የንጉሥ እና የንግሥት ዘውድ ክብ ነው። አራት ማዕዘኑን ያደርጉ ወይም ምንም ያላደረጉ ታሪካቸው በስተመጨረሻ አጉል ነው። ምሳሌ፦ አፄ ዩሐንስ።  
  20.  ጦር ይዞ የግድ ጋሻ መጨመር አለበት። ክብ ከሌለ ትጥቁ አይሟላምና። ለሴቷ መቀነት፣ ለወንዱ ዝናርን መጨመር ይቻላል።   
  21.  ሐበሻ ሲበላ፣ ሲጠጣ፣ ሲያማ፣ ሲያጠቃ፣ ሲወር ወዘተ የግድ ክብ ሠርቶ ነው።   
  22.  ሰውን ሲቀብር የግድ ክብ ሠርቶ በመቆም ነው።  
  23.  ኢትዮጵያ የሚለው ቃል ራሱ ሦስት ክብ ነገር፣ ጎጃም ሦስት፣ ኦሮሞ ሦስት፣ ወላይታ ሦስት፣ ትግራይ ሁለት፣ አማራ ሁለት፣ ሸዋ ሁለት፣ ጐንደር ሁለት፣ አደሬ ሁለት፣ ጉራጌ አንድ፣ አፋር አንድ ክብ ነገር አላቸው።   
  24. ቀን መቊጠሪያው ልክ እንደ ሰዓት በእኩል ሠላሳ ቀናት ተከፋፍሎ ክብ ሠርቶ ሲገጥም አንድ ዓመት ይሆናል።   
  25.  በስፖርት ሜዳ መዞርን (አምስት ሺህ ወይም ዐሥር ሺህ) ወይም ከተማ መዞርን (ማራቶን) የተመለከቱ ስፖርቶች ከሆኑ ማንም አይችለውም። ምሳሌ፦ እንደ እግር ኳስ ያሉ ግን በአራት ማዕዘን ሜዳ፣ በአራት ማዕዘን ግብ የሚጫወቱ ጨዋታዎች መቼም አይቀናውም። በተመሳሳይ መልኩ ገበጣንና ቼዝን ልብ ይሏል።

Friday, March 23, 2018

"ባንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ" የሚለው አነጋገር ታሪካዊ አመጣጥ


"ባንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ" የሚለው አነጋገር ታሪካዊ አመጣጥ
አንዱ ምሁር ነው አሉ አንድ ጊዜ ተይዞ "እግዚአብሔር አለ ብለህ ታምናለህ?" ተብሎ ሲጠይቅ
- ''የለም ብዬ ሄጄ ከሚያፋጠኝ አለ ብዬ ሄጄ ባጣው ይሻለኛል'' አላቸው። ማለት የፈለገው የገባቸው ወንዳታ ይኼ ነው ባንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ማለት አሉና ባንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እስከዛሬ ይላሉ . . .
"የሦስተኛው የዓለም ጦርነት አጀማመር አጭር ታሪክ" ከሚለው መጽሐፌ ላይ የተወሰደ
አቡነ አረጋዊ ቀን 2018

Tuesday, March 20, 2018

የአእምሮ ህሙማን ሆስፒታል ውስጥ ነኝ

ይድረስ ለሁሉም የኔ ቢጤ ታካሚ በሽተኞች በሙሉ፣

አሁን አሁን እንደገባኝ ከሆነ፣ ውልፍጭ ሳንል አርፈን እንቀመጣለን፣ ስክሪኑ ላይ እናፈጣለን፣ ከራሳችን ጋር እናወራለን፣ ብቻችን እንስቃለን፣ ወዲያው እንከፋለን፣ እንቆጣለን፣ ሸብለል፣ ሸብለል እንደገና ፈገግ እንላለን . . .። የታመሙትን አሜን ብለን እንፈውሳለን። ለቅሶ RIP ብለን እንደርሳለን። የወንጌል ቃሉን እንሰብካለን። ቁራዓንን እናስተምራለን። ማርክሲስም ሌኒኒዝም እናስፋፋለን። ሚካኤል ገብሪኤል እያለን የቀን መቊጠሪያ እንሆናለን። ሲለን ደግሞ ቁጭ ብለን መንግሥት እንሾማለን፣ ቁጭ ብለን መንግሥት እንሽራለን። የምንፈልገውን ሰው ከየትኛውም ዓለም ቢሆን አምጥተን እናናግራለን። የጠላነውን ደግሞ ያለበት ድረስ ሄደን አፈር ድሜ እናበላዋለን። የማናውቃቸውም ጓደኞች፣ ቤተ እንስሳት፣ (የአንበሳ ግቢዎች)፣ ትላልቅ የሚያምሩ እርሻዎች፣ ገራሚ ከተሞች፣ በምድር ላይ ያልተፈጠሩ ጉዶች በአእምሯችን ይመላለሳሉ። ውድ ምግብ ቤቶች ገብተን እንመገባለን፣ የሰው ድስት እንቀላውጣለን። ሳንቲም ጠብ የማያደርግ ቢንጎ፣ ካንዲ ካራሽ ምናምን እንጫወታለን። ያልሆነውን እንሆናለን። በሄድንበት ሁሉ ቪዛችንን ከዚሁ እናገኛለን። ቤተሰብ ፈልጎ እንዳያጣን ዳራችንን እዚህ እንተዋለን። ዕድሜያችንን፣ ጠላታችንን፣ ገዳያችንን ሁሉ እናስጠነቁላለን። ሰውን ከመሬት ተነስተን እንወርፋለን፣ እንደ ልባችን እንሳደባለን እንዲሁም ሆኖ ችግር የለውም ብለን እናስባለን። ግድግዳ ላይ እንደምንጽፍ ያለን ፍጹም እንረሳለን። ያልተጨበጠ ወሬ ይዘን እንጨነቃለን፣ እናራግባለን፣ የለጠፍነውን የወደዱትን የለጠፉትን እንወድላቸዋለን፣ ዝም ያሉንን ዝም እንላቸዋለን፣ የሰደቡንን እስከ ዘር ማንዘር እንሞልጫቸዋለን። ፖስት ያደረግነውን ስንት Like እንዳገኘ በጉጉት እንቆጥራለን፣ ጠላትና ወዳጅ እዚያው እንለያለን . . . ረጋ ብላችሁ አስቡበት እስኪ ብታምኑም ባታሙኑም አብደናል፣ ንቀውናል፣ ጨርቅ ጥለን ቶኬ ሆነናል! Facebook ሌላ ምንም ነገር ሳይሆን የአእምሮ ህሙማን መታከሚያ ሆስፒታል ነው። እኛም በሆስፒታሉ ውስጥ ያለን አሊያም ተመላላሽ ወይም ተኝቶ ታካሚ በሽተኞች ነን። አራባ አራት ነጥብ። ። ። ። ። ። እኔ ባለሁበት በዚኛው ዋርድ ዛሬ ማታ ታዋቂ ዘፋኝ የሚገኝበት ፓርቲ ስለደገስኩ አደራ እንዳትቀሩ፣ እንጨሳለን ፒሪ ፒሪ ባጫ ቡጫ ዊሂ ዊሂ ዊሂ

ምንጭ፦

Who is the funniest?

Who is the funniest?

 
1. A man who removed his shoes to enter a taxi.....


2. A man who went to the bank with a spanner to open a bank account.




3. A man who went to bed with a ruler just to know how long he slept


4. A man who watched the news and waved at the news reader.


5. A nurse who woke up a sleeping patient simply because she forgot to give him sleeping pills....


6. A man who lowered his TV volume because he wanted to read a text message..


7. A man who polished his shoes to take a passport photo.


8. A man who climbed a mango tree to check if the mango was ripe enough then came down and started stoning it.....


9. A man who chose to drink Fanta because he thought Sprite was unripe

10. A man who saw something that looked like shit, touched and tasted and said "Hmmm" na shit ooo!!!
Thank God I no march on them....


11. A man who put his radio inside the refrigerator because he wanted to listen to Cool FM...


12. A man who brushed his teeth because he wants to speak to his girlfrnd on phone


Source: unknown from the internet world

http://www.maisondelaradio.fr/evenement/cinema-sonore/illuminations/sur-les-traces-de-rimbaud-en-ethiopie-avec-des-musiciens

Thursday, March 15, 2018

ማሳሰቢያ

ማሳሰቢያ፦ ዶ/ር የሚል ቅጥያ በማየት እንዳትሸወዱ ተብላችኋል። ዶ/ር ሲበተን ዶንቆር ሊሆን ይችላል!!!
ከጽ/ቤቱ (ጽዳት ቤቱ)

Tuesday, March 13, 2018

Some notes on his 44th birthday

Now it is 44 since I joined the drama of this world. I am trying to act my role as much as possible to extent nobody can copy it except may be my kids. I have been climbing the mountain so far and it is also oblivious that the road shall go downhill very soon. Whatever the topography I put my footstep, I enjoy the ride and I also enjoy the company of all the people I came to know on board. Last but not least just to quot someone I admire from the literature world:
“I was brought up to respect my elders, so now I don't have to respect anybody.” 
― George Burns

Thursday, March 8, 2018

Ten good signs if you’re 100% Habesha



Ten good signs if you’re 100% Habesha

You’re 100% Habesha if:

1. At the airport, you are accompanied or received by at least three people.
2. You have sworn to eat Injera in every corner of the world; whatever the cost you will find a means to smuggle it, if forbidden.
3. You always sit closest to the door of your host inviting you to his/her house for the first time.
4. You cannot mingle with other races as long as there are other Habeshas around you.
5. You constantly confuse between “yes” and “no”.
6. You keep collections of plates and glasses in your living room that you will ever and never serve; and also your kitchen is full of things you barely use.
7. You have pictures of dead people on your wall along with the living ones.
8. You are punctual only for one business; no kidding with funerals.  
9. You dare to sacrifice even your life to run away from your country; but when you succeed to do so, you immediately get home sick.
10. You keep on talking after someone says goodbye.

Goodbye for now dear and look at sign number 10 again…