የሺህ ዓመት ለፈጣሪ አንድ ቀን ነው ምሥጢር
አንድ ቀን ለግዜር ከሆነ ሽህ ዓመት
አንድ ቀን ለፈጣሪ ከሆነ ሽህ ዓመት
ላበሻ የግዜር ሰው ድሀ የምትሉት
አክሱምን ገትሮ ጠፋ የምትሉት
ከላሊበላ ወዲህ አልታየም
የፈሰሰ ውሃ አላቀናም
ብላችሁ ያማችሁ
ሥጋውን የበላችሁ
ሲያረፍድ ተቀጠሮ
ቢቀር ተደማምሮ
ሐበሻ የግዜሩ ሰው
ለእምነቱ የሚሞተው
ደቂቃን ቢያደርግ ሰዓት
ቀንን ብዙ ወራት
ወራትን ዘመናት
አሁን ምን አለበት ብትተዉት
ድሀው ተስፋን ቢቆጥርበት
አንድ ቀን ለፈጣሪ ከሆነ ሽህ ዓመት
ላበሻ የግዜር ሰው ድሀ የምትሉት
አክሱምን ገትሮ ጠፋ የምትሉት
ከላሊበላ ወዲህ አልታየም
የፈሰሰ ውሃ አላቀናም
ብላችሁ ያማችሁ
ሥጋውን የበላችሁ
ሲያረፍድ ተቀጠሮ
ቢቀር ተደማምሮ
ሐበሻ የግዜሩ ሰው
ለእምነቱ የሚሞተው
ደቂቃን ቢያደርግ ሰዓት
ቀንን ብዙ ወራት
ወራትን ዘመናት
አሁን ምን አለበት ብትተዉት
ድሀው ተስፋን ቢቆጥርበት
መጋቢት የጊዮርጊስ ቀን 2018 በጊዜ ሲቀለድ
ብሩክ በ.
No comments:
Post a Comment