Thursday, December 28, 2017

ብርጭቆ የሰቀልን ለታ

ብርጭቆ የሰቀልን ለታ

ስፖርት ነገር ትንሽ ጂም ሠራሁ ብዬ 
ቅዳሚት ሰንበትን በጎርደን ጂን አክፍዬ
ከቼቫዝ አብሶልዩት እስከ አፕሬትቭ አረቂ ጠላ
ሁሉን ስሸፍጠው ከብርዙ ጠጅ እስከ አምቡላ
ስደሰት ስከፋ ብርጭቆ ሳነሣ
ስመዠርጠው ለራሴ ሳልሣሣ
ለፓስታ ወይን ስናዝለት ኮንስፓኛን ለጥሬ
ስንታጠብ ውስኪ፣ ከኮኝክ እስከ ካምፓሬ
የለጋነው ሻምፓኝ እሳቱን የጫርንለት ኮክቴል
ቲያ ማሪያው ባካርዲው መች ልኑር ያሰኛል
ዓለምን እሳንሶ በመለኪያ ውስጥ ከቷት
ኢምንት አሳክሏት የመጠጥ ምትሃት
የዋጥነው ታኪላ፣ ሳምቡካና ኳንትሮ
ያኖረልን አልኮል ድሮን በዘንድሮ
ጽዋ እያጋጨን ነገን ዛሬ ሠራነው
ኮማሪን ካጎት ካክስት ፈረጅነው
ሰኞን አጥቁረን ስንቴ ሥራ ቀርን
ስንት ጊዜስ ከሰው መሃል ጎደልን
ቃል አባይ ሆነን ቃላችንን በላን
ለአቅመ ቤት ሳይደርስ እንዲያው በበራሪ
ስንት ደሞዝ ቀረ ከንቱ ወድቆ ከግሮሰሪ
ያ የልብ ወዳጄ የምለው የምሽታ ቤቱ
ከልቡ ሳላድር ሠርክ ሸንቶኝ በሽንቱ
ከሆዱ አራግፎኝ ሲገባ ከቤቱ
የኔ ነው የሱ የማን ነው ጥፋቱ
ደሞ ጠዋት እነሣና እሾህን በእሾህ ብዬ
ስታደም በራሴ የተዝካሬን ድንኳን ጥዬ
በራሴው ደጀ ሰላም መክፈልቴ ሆኖ ቢራ
አዲሱን ቀኔን ሳጨልመው ከፍቼ ዳንኪራ
ወዳጅ ዘመድ ቤተሰብ ሲገታተረኝ
ተስፋ ቆርጦ በኔ ዐይኑን ሲደብቀኝ
ከነ ማሪንጌ ቻ ስንል ቸበርቻቻ
ለኛ ፍቅር ደስታ የት ተገኝቶ አቻ
ቧልስ ቡጊ ቡጊ ዲስኮና ሳልሳ
ዕድሜ በሮ ሄዶ ስንወድቅ ስንነሣ
ያ ደሞ ትልቁ ኮማሪ በኃላፊነት ጠጡ ባይ
አዛኝ ቅቤ አንጓች የእፉኚት ልጅ አስመሳይ
ቀድሞ እሱ ራሱ ራሱን ኃላፊነት ቢሰማው
ንዋይ ባያሰክረው ህሊናውን ባይረግጠው
ለኛ ጠላ ቢራ ባልነበር ጠምቆ የሚሸጠው
የፊደል ገበታን በጠ-ጡ ባልጀመረው
ስካራችን ሆኖ አዳራችን
ሌት ተቀን ሕይወታችን
ከጠጣህ አትንዳ ብለው ደርሶ የሞገቱን
እነሱ አልነበሩ እንዴ ወደዚህ የነዱን
በእባብ አንደበት እንደ ቆሪጥ
አመላክተው አቅጣጫ
ጡጦ አስጥለውን ሲግቱን መጠጥ
አድባራቸውን ልናሞቅ ስንንጫጫ
ይኸው ኖረን ኖረን ስንጨልጥ ስንለጋ
መድከም አይቀር ከጠላነው አልጋ፣
የማታ ማታ ስንዘረጋ
ኮሮሸራችን ሲያዝ ሲያብይ ጉልበታችን
ጽልመቱን አልብሶን ሲያበራ ጉበታችን
ጥፋቱ የማን ነው ውሃን የተውን ለታ
የጥፋት ውሃ ሲወስደን የማታ የማታ
ውሃ ሲወስደን አሳስቆ
ከሰው መሃል ነጥቆ
ድንገት ደርሶ ጎርፉ ሲወስደን አንቦጫርቆ
ውስጥ ውስጡን ገሎን ሥራውን አጠናቆ
ባንገት እስኪከትልን ሸምቀቆ
ሞት ሲፈርደን ማን ሰምቶ፣ ማን ዐውቆ
ቀምቅሜ ፈጅቼው
ጤናዬን በገንዘቤ
ልሄድ ነው መሰል
ገንዘብን ተገንዝቤ
ካለቀ በኋላ ከደቀቀ
ክፋትሽ ታወቀ
አዲዮስ ግሮሰሪ
እያማርሽኝ ቅሪ
ብርጭቆ የሰቀልን ለታ
ሆን-ለት የራሳችን ጌታ

ትሳስ 12 ዕለተ ሚካኤል 2017

Tuesday, December 26, 2017

ቅኔ ብጤ አማረኝ . . .


ውሻሉ ዶክተር ይኼው፣ ጊዜው ደርሶ ተኛ
ማረጉ ከበደው ለራሱ፣ እንዳያርግ እንደኛ
ትህሳስ 17፣ 2017 በእስጢፋኖስ ሰማዕቱ ከመዲናይቱ

Friday, December 22, 2017

ቁንጫና ትዃን


ቁንጫና ትዃን 
አንድ ግንባር ፈጥረው
ጠላትን ሊመቱ አብ-ረው
ቃል ኪዳን ተሳስረው
ሲወረዱ ከጦሩ ሜዳ
ከፍልሚያው አውድማ
ምድር ስትዘል ሰማይ 
ረመጥ እሳት ላይ ቆማ
የጠላት ክንድ በርትቶ
የሞት ሞቱን 
ድንገት ተነሥቶ
ሲወረወር ሲወናጨፍ 
ከአጥናፍ አጥናፍ
በግራም በቀኝም 
ሲነፋ የእሳት ወናፍ
ቁንጮች በስልት አፈግፍገው
ሲያመልጡ ተፈናጥረው
ናፍጣ እንደ ጨረሰ ታንክ
ሲንተፋተፍ ሲንዘባዘብ
መች ታየው ትዃን 
በጠላት ሲከበብ
ትዃን ሞኙ
ቁንጫ አማኙ
እንዲያው እንደ በሬ 
ሣሩን ብቻ ዐይቶ 
ገደሉን ረስቶ
ልቡን ለሸማቂ 
እንካ ብሎ ሰጥቶ
አጓጉል ተሰውቶ
እንዲያው በአጉል ቀን 
ከሸማቂ ጋር ዘምቶ
ታየ ከሜዳው ላይ 
አከርካሪውን ተመትቶ
ለስትራቴጂያዊ ጠላት
ስትራቴጂያዊ ወዳጅነት
አጉል ጅራትን ማሳየት
ላይቀር ኋላ መበላላት
11/04/2017 ታህሳስ

Friday, December 15, 2017

Dedication to my Cathedral friends (brothers) from Childhood till today before it is too late on re-birth of mine


Dear Brothers and Sisters I have a dedication or rather a gift for you all. Thank you for all your support you gave during my fight against the odds and finding my true self. Each one of you had an important role in changing my life. I just thank God for giving me these blessing: the love and trust of you all. Thank you for your patience and encouragement whatever the situation was. I am now a different Brook, no kidding. Merci a vous tous! Amesgenallehu! Yekeneyley! Geletoma! Shukeren! Danks! Grace mille! And with all other languages of the world and the heaven. My gift to you is a quot that I found from great quotations of Bob Marely. I also translated it.

“Only once in your life, I truly believe, you find someone who can completely turn your world around. You tell them things that you’ve never shared with another soul and they absorb everything you say and actually want to hear more. You share hopes for the future, dreams that will never come true, goals that were never achieved and the many disappointments life has thrown at you. When something wonderful happens, you can’t wait to tell them about it, knowing they will share in your excitement. They are not embarrassed to cry with you when you are hurting or laugh with you when you make a fool of yourself. Never do they hurt your feelings or make you feel like you are not good enough, but rather they build you up and show you the things about yourself that make you special and even beautiful. There is never any pressure, jealousy or competition but only a quiet calmness when they are around. You can be yourself and not worry about what they will think of you because they love you for who you are. The things that seem insignificant to most people such as a note, song or walk become invaluable treasures kept safe in your heart to cherish forever. Memories of your childhood come back and are so clear and vivid it’s like being young again. Colours seem brighter and more brilliant. Laughter seems part of daily life where before it was infrequent or didn’t exist at all. A phone call or two during the day helps to get you through a long day’s work and always brings a smile to your face. In their presence, there’s no need for continuous conversation, but you find you’re quite content in just having them nearby. Things that never interested you before become fascinating because you know they are important to this person who is so special to you. You think of this person on every occasion and in everything you do. Simple things bring them to mind like a pale blue sky, gentle wind or even a storm cloud on the horizon. You open your heart knowing that there’s a chance it may be broken one day and in opening your heart, you experience a love and joy that you never dreamed possible. You find that being vulnerable is the only way to allow your heart to feel true pleasure that’s so real it scares you. You find strength in knowing you have a true friend and possibly a soul mate who will remain loyal to the end. Life seems completely different, exciting and worthwhile. Your only hope and security is in knowing that they are a part of your life.”
― Bob Marley

“በሕይወት ዘመንህ ሁሉ አንድ ጊዜ ብቻ ዓለምን ሁሉ እንደ አዲስ የሚፈጥሩልህን ሰዎች ታገኛለህ ብዬ ከልቤ አምናለሁ። ከሌላ ነፍስ ጋር ያልተጫወትካቸውን ነገሮች ትነግራቸዋለህ እና የምትናገረውን ሁሉ አጣጥመው ይውጡታል ብሎም እንደገና ተጨማሪ ነገር እንድታወራላቸው ይፈልጋሉ። የወደፊት ተስፋህን፣ ምን ጊዜም ዕውን የማይሆን ሕልምህን፣ ግብ ያልመቱ ዕቅዶችህን፣ ሕይወት ባንተ ላይ የወረወረቻቸውን አስቀያሚ ነገሮችን ሁሉ ታጫውታቸዋለህ። የሆነ አስደናቂ፣ ግሩም ነገር ሲፈጠር አግኝተህ እስክትነግራቸው ስሜትህን መቆጣጠር ያቅትሃል፣ የደስታህ ተካፋይ እንደሚሆኑ ልብህ በእርግጠኝነት ይነግርሃል። ስትጎዳ አብረውህ ለማልቀስ ሐፍረት አይገታቸውም፣ ራስህን ቂል ስታደርግ ካንተ ጋር አብረው ከመሳቅ ወደኋላ አይሉም። በጭራሽ ስሜትህን አይጎዱትም ወይም የማትረባ ሰው እንደሆንክ ሆኖ እንዲሰማህ አያደርግሁም፤ ይልቁንስ የጎደለህን ነገር እየሞሉ ያገዝፉህና አንተን ልዩ ሰው የሚያደርጉህን በጎ ጎኖችህን ብሎም ውበትን የሚያጎናጽፉህን ጌጦችህን ከላይህ ላይ አጉልተው በማውጣት መልሰው ላንተ ያሳዩሃል። በግድ አንድን ነገር እንድትቀበል ማስገደድ፣ ባንተ ላይ ምንቀኝነት ሆነ ቅናት፣ ካንተ ጋር ተራ ፉክክር ቦታ አይኖራቸውም፤ ይልቁንስ እነርስሱ አጠገብህ በሚኖሩበት ጊዜ በቦታው ላይ ጸጥታ የተሞላ ፍጹማዊ እርጋታ ይነግሣል። በማንነትህ ብቻ ስለሚወዱህና ራስህን መሆን ስለምትችል ስላንተ ምን እንደሚያስቡ ሙሉ በሙሉ አለመጨነቅ ትችላለህ። የሙዚቃ ኖታ፣ ዘፈን ወይም በእግር ሽርሽር ማድረግ የመሳሰሉ እዚህ ግቡ የማይባሉ ተራ ነገሮች ሁሉ በፍቅር የምትወዳቸው፣ ገንዘብ የማይገዛቸው፣ በስስት የምትይዛቸው፣ ውድ ሀብቶችህ ሆነው በልብህ ሕያው ሆነው ለዘላለም ይኖራሉ። የልጅነት ጊዜ ትዝታዎችህ ተመልሰው እንደገና ይመጣሉ እና ሲመጡም ምንም ብዥታ የሌለባቸው በግልፅ የሚታዩ ይሆናሉ፤ በቃ መልሶ ወደ ልጅነት እንደገና የመመለስና ልጅ የመሆን ያክል ነው። ቀለማት ከበፊቱ ይልቅ ደምቀውና አንጸባራቂ ሆነው ይታዩሃል። ከዚህ ቀደም ሣቅ በስንት አንዴ በመከራ ይከሰት እንዳልነበር ወይም ከናካቴው ጠፍቶ እንዳልነበር የዕለት ተዕለት ተራ ጉዳይ ይሆንልሃል። አንድ ጊዜ ወይም ሁለቴ ስልክ መደወል ረዥሙን ቀንህን በድል እንድትወጣው ያግዝሃል እና ሁልጊዜም ስልኩን ስትዘጋውም ፊትህ ላይ ፈገግታን ይቀራል። ጓደኞችህ ባሉበት፣ ዝምብሎ ሳያቋርጡ ወሬ ማውራት ግድ አይልም፤ በቃ አጠገብህ ስላሉ ብቻ ሐሴትን ታደርጋለህ። ላንተ በጣም ልዩ ለሆነው ሰው በጣም አስፈላጊ ቁምነገሮች እንደሆኑ ስለምታውቅ ከዚህ ቀደም ደንታ የማይሰጡህ የነበሩ ነገሮች አሁን ግን አስደሳች ይሆኑልሃል። ስለዚህኛው ሰው በሁሉም አጋጣሚ እና በሁሉም የምታደርገው ነገር ሁሉ ታስታውሳለህ። ተራ ነገሮች እንደ ደብዘዝ ያለ ሰማያዊ ሰማይ፣ እንደ በሽውታ ቀስ ብሎ የሚነፍስ ነፋስ፣ ወይም በአድማስ ላይ ውሽንፍር እንደ ቀላቀለ ዝናብ እነርሱን ወደ እዝነ ልቦናህ ያመጣቸዋል። ሊሰበር ሊችልበት ዕድል መኖሩን እያወቅክ ልብህን ተከፍተዋለህ እናም ስትከፍተው ሊኖር ይችላል ብለህ አስበህ የማታውቀውን ፍቅር እና ደስታ አገኝተህ ታጣጥማቸዋለህ። በጣም እውነት ከመሆኑ የተነሳ የሚያፈራህን እውነተኛውን ደስታ ልብህ እንዲያጣጥም ለማድረግ ብቸኛው መንገድ ራስህን ለአደጋ ተጋላጭ ማድረግ እንደሆነ ታረዳዋለህ። እውነተኛ ጓደኛ እንዳለህ ምናልባትም እስከ መጨረሻው ካንተ ጋር በታማኝነት የሚዘልቅ የነፍስህ አማሳያ እንዳለ በማወቅህ ጥንካሬን ታገኛለህ። ሕይወት ሙሉ በሙሉ ፍጹም ሌላ መስላ፣ አስደሳች እና ቢያጣጥሟት የማትጎዳ ሆና ትታይሃለች። ተስፋ ብቻ ታደርጋለህ እና የደኅንነት ዋስትናህ ጓደኞችህ የሕይወትህ አንድ አካል መሆናቸውን ማወቅ ብቻ ነው።”

ቦብ ማርሊ

Wednesday, December 13, 2017

Miss Me But Let Me Go [Translated into Amharic as a dedication to Ras Empis Fred, the great French artist]



A picture containing photo, building, indoor

Description generated with high confidence
Miss Me But Let Me Go
                [To Sir Fred]


When I come to the end of the road
And the sun has set for me
I want no rites in a gloom-filled room
Why cry for a soul set free?

Miss me a little-but not too long
And not with your head bowed low
Remember the love that we once shared
Miss me-but let me go

For this is a journey that we all must take
And each must go alone.
It's all part of the Master's plan
A step on the road to home

When you are lonely and sick of heart
Go to the friends we know
And bury your sorrows in doing good deeds
Miss me but let me go.


Author: Anonymous English Poem
Translation in Amharic By Brook Beyene
To my beloved brother His Honor Great Artist Empis Fred (Ras Fredo), and his beloved spouse Ariane Le Lay, the lover of Ethiopia and Ethiopians
On the day of his last journey out today December 13, 2017
እቴ ትንሽ ናፍቂኝ፣ ግን ልሂድበት! እዚህ ቆይ አትበይኝ

ለአያ ፍሬድ


ከመንገዱ ጫፍ ላይ ስደርስ፣ መንገዴ ሲያልቅ
ፀሐይዋ ከሰማይ ለእኔ ስታዘቀዝቅ ልትጠልቅ
ደብዛዛ ብርሃን በተሞላ ቀዬ፣ አያሻኝም ፍትሃት
ለነፍስ ምን ያረጋል ለቅሶ፣ አግኝታ ሳለ ሃርነት?


ትንሽ ብቻ ናፍቂኝ ብዙ እንዳይሆን ግን አደራሽን
ባጎነበሰ አንገትሽ ሸጉጠሽ፣ እንዳትቀብሪው ፊትሽን
ስላለፈ ፍቅራችን ብለሽ፣ መቼም እንዳትረሺኝ!
እቴ ትንሽ ናፍቂኝ፣ ግን ልሂድበት! እዚህ ቆይ አትበይኝ


እነሆ ዛሬ ተራዬ ደርሶ መሳፈር አለብኝና ለዚህ ጉዞ
ለብቻ እንጅ፣ አይኬድምና እዚህ፣ እጅ ለእጅ ተያይዞ
እንደ ፈጣሪያችን ዕቅድ ሐሳብ፣ አንዱ መገለጫ ምክንያት
ከዋናው ቤታችን ለመድረስ፣ ይኸው አንድ እርምጃ ወደፊት


ብቸኝነት ሲውጥሽ ሲከፋ ክፉኛ ልብሽ
ጓደኞቻችን እንደኔ፣ ላንቺ ዛሬም አሉልሽ
እናም ያን ሐዘንሽ ገንዘሽ፣ በጎ ሥራ እየሠራሽ ቅበሪልኝ
እቴ ትንሽ ናፍቂኝ፣ ግን ልሂድበት! እዚህ ቆይ አትበይኝ



ደራሲው ያልታወቀ የእንግሊዝኛ ግጥም
ትርጉም በብሩክ በየነ
ለውድ ወንድሜ ክቡር ታላቅ አርቲስት
ኤምፒስ ፍሬድ (ራስ ፍሬዶ) እና ለውድ ባለቤቱ ኧሪያን ለ ሌይ፣
የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን ወዳጅ በዕለተ ሕልፈቱ ዛሬ ታህሳስ ፬፣ ፳፻፲








Sunday, August 6, 2017

ሰው ሆይ ስማ!

ሰው ሆይ ስማ! መቼም ስለማትሰማ
ሰው ሆይ ስማ! ጆሮህ ስለማይረባ
ሰው ሆይ አትስማ! አሁን ስለምትሰማ
የሚያገባህን ትተህ በማያገባህ ስትገባ
መታሰቢየነቱ ለአባባ ተስፋዬ ሐምሌ 30, 2017 ያው ወደ ኋላ አልቀርም

Friday, August 4, 2017

ጠጡ






ጠጡ!

ቅዱስ ሆሄያት . . . በፊደል ገበታ መባቻ ሠመሩ




ለሰው ልጅ ሁሉ. . . ጠቃሚ አግባቢ ቃል ሠሩ


. . . ጠ-ጡ !
. . . ጠ-ጡ !

 . . . ጠ-ጡ!


ታለም ስትመጡ ጠጡ ሽርት ውሀ

ባለም ስትኖሩ ጠጡ የግዜር ውሀ

ሻይ፣ ቡና፣ አረቂ፣ ሌላም ብዙ ብዙ

ጠጡ ጨልጡት ዋንጫውን ያዙ

ግን አደራ የራሳችሁን ብቻ ጠጡ

መዘዝ አለው የሰው አትቀላውጡ

መርዝ፣ ደም፣ ጥይት እንዳትጠጡ

ጽዋችሁን ብቻ ጠ-ጡ!

 



የካቲት ፳፪፣ ፳፻፲፰


Albert Camus

አንድና አንድ ብቻ ያልተመለሰ ከባድ የሥነ አስተሳሰብ ጥያቄ አለ፦ እሱም ራስን የማጥፋት ጉዳይ ነው። ሕይወትን መኖር ወይም አለመኖር ልክ ነው ወይም አይደለም ማለት መሠረታዊውን የሥነ አስተሳሰብ ያልተመለሰ ጥያቄ ከመመለስ ጋር ይስተካከላል። ---- አልቤር ካሙ "የሲሲፈስ ምሥጢር" (1942)

Wednesday, July 5, 2017

ላይ ከራስ ዱሜራ. . .




ላይ ከራስ ዱሜራ፣ ራስ ካሳር አቋርጦ ሃገረ ኤርትራ
የኑብያ አሸዋን ጠፍጥፎ በናስር ውሃ ጋዛ ፒራሚድ የሠራ
ካታንጋ ከታላቁ ካሮ ኬፕታውን ኮይኮይና ሳን ስልተ ቀመሩ
ታች ካልሃሪ፣ ሳህራ፣ ቲምቡክቱ ሰንጥቆ ዳካር ጫፍ ድንበሩ
ሰፊው እግሬ አንድ አገር በአንድ ጊዜ ረጋጩ
ጣና፣ ቪክቶሪያ፣ ቮልታ፣ ቻድ ውሃ መጣጩ
ከኪሎማንጃሮም በላይ የሰፋ፣ የረዘመ ደረቴ
ከነዳሽን፣ ከነካሜሩን በላይ የዘለቀ አንገቴ
በቀኝ አንድሮሜዳን ጨብጦ በግራ ስድስቶ
አፍሶ የሚያድር እጄ ከዋክብት አስፈርቶ
ጠቆር ብዬ ቡና፣ እልፍ ምእልፊት ደቂቃኑን የማቃና
ራሴ ላይ የሚታሰረው ምልክት የሰማዩ ቀስተ ደመና
ልቤ ገር ስንት አገር አስልጦ፣ አሳልጦ ሳይገዛ ተገዢ
ደሜ እንዲሁ ደመ መራር ሕዋሱ እንደ ፍል ተባዢ
የጥፍሬ ጥጋጥግ ረዝሞ ጥቁር የቀለመው
ሜዳና ሸንተረር ጋራ ቧጭሮ የሚያፈርሰው
በቶም ቶም ጉባዔ ቃና ባልፉን ካሊምባ መትቼ
በኮራ ገመድ ክራር ማሲንቆ ራሴን አጫውቼ
ድቤ አታሞ ከበሮውን ጀምቤውን ደብድቤ
ስለው ዳንሱን በድንበር በአጥር መች ተገድቤ
ሺ አፍሼ ሺ የምዘራ ዛፎችን በአንድ እፍኝ ቀጣፊ
የእግዜሮች ባርያ ታማኝ ጥቁር አጋፋሪ ጥቁር አሳላፊ
ምሥጢሬን ሳንሶላስል በዜማ በዳንኪራ
የጠራች እውነት በራሴ ኩራዝ ሳበራ
እነማን ቀድመው ሰሙ? እነማን ቀድመው ሰገዱ
ወይስ ስተው፣ ነጭ እንዲቀልም ጥቁር ሰው አረዱ?  

ዕለተ አማኑኤል ሰኔ፣ 2017