Tuesday, June 4, 2019

በሕይወትህ በጥብቅ ልታከብራቸው የሚገቡ ስድስት ግላዊ መመሪያዎች፦


1. ብቻህን ስትሆን ፥ ሐሳብህን ተቆጣጠረው።
2. ከጓደኞችህ ጋር ስትሆን ፥ ምላስህን ተቆጣጠረው።
3. ንዴት ላይ ስትሆን ፥ ቁጣህን ተቆጣጠረው።
4. ከሌሎች ጋር ስትሆን ፥ ዓመልህን ተቆጣጠረው።
5. ችግር ላይ ስትሆን ፥ ስሜትህን ተቆጣጠረው።
6. ፈጣሪ በረከቱን ሲሰጥህ ፥ ራስ ወዳድነትህን ተቆጣጠረው።
ትርጉም ከከሣቴ ብርሃን ቡሩክ
ምንጭ፦ #Daily Prayers
Image may contain: text

Thursday, April 18, 2019

«ጌ» ፊደል እና ትርጉሙ


«ጌ» እና ትርጉሙ
የ«ጌ» ትርጉም - እንደ «ጋ» (እዚህጋ፣ እዚያጋ ወዘተ) በቃል መጨረሻ እየገባ ምድር ቦታ ስፍራ ተብሎ ይተረጐማል። (ማስረጃ እጅጌ፣  ባለጌ፣  ገደልጌ፣  ገዳምጌ፣  ጕራጌ፣  ግርጌ፣  ደረስጌ፣  ወገብጌ ዋንዛጌ፣  ሐረርጌ፣  ይተጌ፣  ላምጌ፣  ንብጌ፣  ዐዲስጌ፣  ዕጨጌ (ሐፄጌ)  ዐምባላጌ፣  ዐንገትጌ፣  ፍንጥርጌ፣  ቅዱስጌ፣  ራስጌ፣  ሰላምጌ የኹሉንም ትርጓሜ በየስፍራው ከዚህ በታች ይመለከቷል። ትግሬ ሐባብም አገርን ድጌ ይለዋል።
እጅጌ = 1. የእጅ፣  ማግቢያ ፤-እጅ። 2. የእጅ ልብስ ወይም እጁን እንዳይበርደው የእጅ ማጥለቂያ በቀሚስ ላይ የሚሰፋ እጅጌ የእጅ ልብስ።
ባለጌ = 1. አግድሞ አደግ፣  ስድ፣  መረን፣  ያልተቀጣ፣  ያልተገሠጸ፣  ነውረኛ፣  ነውር ጌጡ አያት ያሳደገው ልጅ። «ባለጌን ካሳደገው የገደለው ይጸድቃል።» ወይም «ባለጌ የጠገበ ለት ይርበው አይመስለውም።» እንዲሉ። 2. ባለምድር ፤ -ባለገ 3. ያልተቀጣ ሕገ ወጥ ነውር ነቀፋ የሚኾን ነገርን የሚሠራ። 2. «ጌ» ቦታን አመልካች ነው ለጊዜው የነቀፋ ስድብ ስም ይመስላል ባላባት ባለርስት ማለት ነው። «ጌ» ማለት ቤት ማለት ነው። ባላባት ባለርስት ለማለት ባለጌ ይባል ነበር ዱሮ።
ገደልጌ = በይፋት ያለ ቀበሌ ገደላም ምድር
ገዳምጌ = በታች ወግዳ ያለ አገር የገዳም ምድር ማለት ነው።
ጕራጌ = 1. ክፍል፣  የጕራጌ አገር። ቤት ጕራጌ እንዲሉ። በዝርዝር ሲቈጥሩት ግን ነገዱና አገሩ እስከ ፳፭ ይደርሳል። 2. የውል ስም የጉራጌ ሕዝብ ወይም የጉራጌ አገር ከጕርዐ ፈልሰው ወደ ጉራጌ አገር መጥተው ሰባት ቤት ጕራዐጌን ወልደው የሚኖሩ ሕዝብ ናቸው።
ግርጌ = የእግር፣  ስፍራ -እግር
ደረስጌ = ደረስጌ ማርያም ደባርቅ፣ ጎንደር ውስጥ ደረስጌ (ደብረ-ስጌ ከሚለው ስም የመጣ)፣ እሚባል ቦታ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ነው። በዘመነ መሳፍንት ገነው የነበሩት ደጃች ውቤ እራሳቸውን ለማንገሥ ሲሉ የጀርመኑን ሠዓሊ እና ሳይንቲስት ዶክተር ሺምፐር በመቅጠር 1840ዎቹ መጀመሪያ ያስገነቡት ቤተክርስቲያን ነው። በኋላ ላይ ከወደፊት ዓፄ ቴዎድሮስ ጋር በዚሁ አካባቢ ጦርነት ገጥመው ስለተሸነፉ፣ ራስ ውቤ ለሥርዓተ ንግሣቸው ባሠሩት ቤተ ክርስቲያን ዓፄ ቴዎድሮስ በአቡነ ሰላማ እጅ ተቀብተው ዘውድ ጭነው ነገሡበት። ይሄውም 1847 መሆኑ ነው። 2. አጼ ቴዎድሮስ ንግሥናቸውን ያወጁበት ሰገነት፣ ስሜን ጃናሞራ፣ ደረስጌ ማርያም
ወገብጌ = 1. ጥብጣብ፣ ቀበቶ የሚገባበት፣  በስተላይ ያለ ውስጠ ክፍት፣  የሱሪ ጫፍ፣  በወገብ ላይ የሚውል የወገብ ስፍራ። 2. የሱሪ ጥብጣብ ሙያ ስፌት በወገብ ላይ የሚውል ነገር ኹሉ ወገብጌ ይባላል።
ዋንዛጌ = የዋንዛጌ ( ዋንዛ) ትርጉም - ያገር ስም፣ በታችኛው ወግዳ ሰሜን በተጕለት ያለ አገር። ዋንዛ ያለባት ምድር ማለት ነው።
ሐረርጌ = ሐረር ለዐዲስ አበባ ምሥራቅ የሚኾን ብዙ አውራጆች ያሉት ትልቅ ከተማ። የሐረርጌ ፤ (ሐረር - ጌ) ትርጉም - ምድረ ቈላ፣  በረሃ፣  ከአዋሽ ማዶ ያለ አገር፣ የዱሮ ዘመን ጠቅላይ ግዛት።
ይተጌ = የእተጌ ትርጉም  -ይተጌ -እት ፤ የምድር እመቤት። የእተጌ (ዎች) ፤ እኀተ ሐፄጌ) ትርጉም - ይተጌ፣  ንጉሥ፣  እቴ የሚላት፣  የንጉሥ ሚስት፤ ባለኩል፣  ርስቱን፣  ጕልቱን እንደ እት፣  ተካፍላ የምትገዛ፣  የሴት ንግሥት። (ግጥም) ዐሊ ማን ይላታል ሲጠራ እናቱን ፤ እኛስ እንላለን እተጌ መነን። እተጌ ሰብለ ወንጌል፣  እተጌ ጣይቱ እንዲሉ። ጌን ተመልከት። አና፣  የ፣  ተወራራሽ ስለ ኾኑ እተጌ፣  ይተጌ ተብሎ ይነገራል።
ላምጌ = ፎገራ ውስጥ ከደራ አጠገብ ያለች መንደር።
ንብጌ = አገር -ናበ። ንብ ያለበት አገር በቡልጋ ውስጥ የሚገኝ። የግእዝ መጽሐፍ መሐግል ይለዋል ፤ ማሰሪያ ማለት ነው።
ዐዲስጌ = በተጕለት ወስጥ የሚገኛ አገር ከዜጋ ወደም በስተግራ ያለ ቀበሌ። (ሐዲስ - ጌ) ሐዲስ የሚባል ሰው ምድር።
ዕጨጌ (ሐፄጌ) = አቡን ጳጳስ። (ግጥም) መኳንንቱ ሠለጠኑ የጨጌን አገር እመኑ። እኔ የምፈራው ይህነን ካቡን በላይ መኾን። የምድር ዕጮኛ ፤-ዐጨ ፤ ዕጨጌ። 2. የምድር፣ ዕጮኛ ፤ -ዐጨ። 3. [ነገር ስም] የወላይታ ቋንቋ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በወላይታ አገር ሞተሌሚ የሚባለውን ንጉሥ አስተምረውት ከዐረመኔነት ወደ ክርስትና ስለ መለሱት የወላይታ ሐዋርያ ለማለት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጨጋ ይሉአቸው ነበርና እጨጌ ከዚያ ከወላይታ ቋንቋ የተወረሰ ቃል ነው። 4. የደብረ ሊባኖስ ገዳም መምህር ዕጨጌ ሊቀ ካህናት ከመንግሥት ሲሶ ግብር መቀበል።
ዐምባላጌ =  1. በትግሬ ግዛት በደቡብ የሚገኝ ትልቅ ጋራ አምባ። 2. የዐምባላ ምድር ፤ አገር። ዐምባ ዐላጊ ቢል ግን ትርጓሜው ሌላ ነው። 3. በትግሬ ግዛት በደቡብ የሚገኝ ትልቅ ጋራ አምባ።
ዐንገትጌ = 1. ያንገት ስፍራ ፤ ዐንገትን የሚሸፍን የእጀ ጠባብና የቀሚስ የጥብቆ ክሣድ ፤ በስተላይ ያለ ጫፍ (ዘፀ ፳፰፡፴፪)። 2. በአንገት ላይ የሚውል ልብስ የካፖ የኮት የእጀ ጠባብ ቅንፋት (ክሳድ) የሚውልበት አንገትጌ ይባላል።
ፍንጥርጌ = በጠራ ውስጥ ያለ ቀበሌ የፍንጥር ምድር ማለት ነው።
ቅዱስጌ = በቡልጋ አውራጃ ያለ አገር የተቀደሰ ምድር ወይም (ቅዱስ - ጌ) አንድ ቅዱስ የኖረበት የጸለየበት የሰበከበት የቅዱስ አገር ምድር ማለት ነው። ነገር ግን ምድር የምትነገረው በሴት አንቀጽ መኾኑን አስተውል።
ራስጌ = 1. በስተራስ በኩል ያለ ስፍራ የግርጌ አንጻር። 2. [ነገር ስም] ከወደላይ የሚኾን ነገር በመኝታ ጊዜ ራሱን የሚያሳርፍበት ወደ ራስ ወገን
ሰላምጌ = (ሰላምጌ ማሪያም) የሰላምጌ ማርያም ቤተክርስትያን በሰቆጣ ወረዳ 031 ቀበሌ ሰላምጌ በተባለ ጎጥ የምትገኝ ጥንታዊ ቤተክርስትያን ነች። ሰላምጌ ማርያም ስያሜዋን ያገኘችው እዚያው ቀበሌ ውስጥ ከሚገኝና ‹‹ የሰላም ዋሻ ›› የሚል ትርጉም ከተሰጠው ዋሻ ነው። ለዐርባ ዓመታት በዋሻው ውስጥ እንደቆየችና በኋላ ግን ሲራክ የሚባል መነኩሴ ድንኳን በመትከል አስቀመጣት ኋላ፣ ኋላ 12 መነኩሳት ደግሞ የየራሳቸው ባለ አንድ ክፍል የጸሎት ቤት በመትከል መግቢያም መውጫም ያለው በር በመሥራት የጸሎት ያደርሱ ነበር በዚያን ግዜ እነዚህ 12 ጸሎት ቤቶች ተገጣጥመውም 12 ክፍሎች ያሉት እቤተ መቅደስ ሆኑ። ይህም ቤተ መቅደስ የተሠራው ከክርስቶስ በፊት እንደሆነ ይነገራል ዐሥራ ሁለት ክፍሎች ዛሬም ድረስ በቤተክርስትያኑ ህንፃ ውስጥ ይገኛሉ። የጥንት አሠራራቸውም ሆነ የሚሰጡት አገልግሎት አልተቀየረም። የሰላምዕ ማሪያም ቤተክርስቲያን የዉስጥ ክፍል ለዊያዊን ካህናት ከክርስቶስ ልደት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ በሕገ ኦሪት አምልኮተ እግዚአብሔር የሚካሄድባቸው ቤተ እምነቶችን እንደሠሩ በታሪክ ይወሳል። ከነዚህም መካከልም ጣና ቂርቆስ፣ መርጡላ ማርያም፣ ደብረዳምና ተድባበ ማርያም የሚጠቀሱ ናቸው። ሰላምጌ ማርያም ከእነዚህ አቻ እድሜ ያላትና በሕገ ኦሪት አምልኮት እግዚአብሔር ይካሄድባት እንደነበረ እና ከአክሱም ጽዮን ቀጥላ በዘመነ ኦሪት ከተሠሩ ቤተ እምነቶች አንዷ እንደነበረች በታሪክ ይነገራል። ሰላምጌ ማርያም የበርካታ ጥንታዊ ቅርሶች ባለቤት ነች። ጥር 21 የንግሥ በዓሏ ነው።
ድጌ =  1. መቀነት ፤-ደገደገ። 2. [ነገር ስም] ሃያ ዐምስት ወይም ሠላሳ ክንድ የሚሠራና ወንድ ወደ መንገድ ሲሔድ የሚታጠቀው (አስ) ድጉን ሸብ አደረገ (መቀነት ([ግዕዝ])። (ከግእዝ በቁሙ መቀነት የሆድ ካሳ የወገብ ምሳ ወገብ የሚያጠና የሚደግፍ። መቀነት)

በከሣቴ ብርሃን ከዚህም ከዚያም የተቀነበበ

Saturday, March 30, 2019

Facebook በእኔ ዕይታ


(ያልተከሸነ ረቂቅ ጽሑፍ)
ለአብዛኛው አንኮ የኛ ትውልድ Facebook ላይ ያለው ቁምነገር በአጭሩ እንዲህ ነው፦

"እይ፥ ተመልከት ሕይወቴ ካንተ የተሻለ ነው። ምንም ልጻፍ ምን ፣ ሳትወድ በግድህ አንብብ ! እኔ ካንተ የተሻለ አውቃለሁ። ይኼን እውነት ማለትም እኔ ካንተ የተሻለ እንደማውቅ አንተም አሳምረህ ታውቃለህ። አይደለም ብለህ ግን አንዲት ቃል ትንፍሽ ብትል እስከ ዘር ማንዘርህ አጥረግርጌ እሞልጭኸለሁ።" በሚል ጠብ ያለሽ በዳቦ ጭብጥ የተሞላ ዘመናዊ ታዳሚውን አሳታፊ ጉራና ሽፍጥ የተሞላ መደዴ ተውኔት ነው።

እንደሚታወቀው የፌዝቡክ (ግድፈቱ ለነገር ነው) ፈልሳፊውና ባለቤት ከነጓደኞቹ ሐሳቡ የመጣላቸው በመጸዳጃ ቤት ግድግዳ ላይ ከሚለቀለቁ ጽሑፎች እንደሆነ ዓለም ያወቀው ፀሐይ የሞቀው የአደባባይ ምሥጢር ነው። ይህ አባባል በቻይንኛ ፈስ-ቡክ (አሁንም ግድፈቱ ሆን ተብሎ ነው) ፖፖና ውኃ ፍሳሽ የሌለው በሳይበር ቴክኖሎጂ በየጉራንጉሩ የሚገባ የመፀዳጃ ቤት ፍሳሽም ነው ማለት ነው። ምን ለማለት ተፈልጎ ነው ፥ ብዙ ሰዎች በአደባባይ ማለት ወይም መናገር የማይፈልጉትን ወይም ማድረግ የማይችሉትን እንዲናገሩና እንዲያደርጉ ዕድል ተሰጥቶዋቸዋላ!

ፌዝቡክ ሆነ ፈስቡክ እንዲህ እንደ ዛሬው መለስተኛ ምናባዊ የጦር አውድማ ከመሆኑ በፊት፣ እንዲህ እንደ ዛሬው ራሱን የቻለ ስድስተኛ መንግሥት ከመሆኑ በፊት አጀማመሩ ላይ እንደ ዓላማ አድርጎ የተነሣው የተጠፋፉ ጓደኛሞችን ማገናኘት፣ ከዘመድ አዝማድ እንዲሁም ከባለንጀሮችና ዕውቂያዎች ጋር ወቅታዊ የግል መረጃን በመለዋወጥ እንደተቀራራቡ መቆየት የሚያስችል ቅንነት  ያለው የሚመስል አዲስ የቴክኖሎጂ እመርታ ነበር። (ድርጅቱ የሰዎችን ገመና እየሸጠ ድንቡሎ ግብር ሳይከፍል ቢሊዮኔር መሆን መቻሉ ምሥጢር ለጊዜው ይቆይልን።)

መተግበሪያው ሳይውል ሳያድር ግን እንደ ፔን ፍሬንድ የመሳሰሉ ጥንታዊ ከአዲስ ሰው ጋር መተዋወቂያ መድረኮችን ሁሉ በመተካት፣ በቅፅበት ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ጓደኛ ተብዬ የፌዝቡክ ጀሌዎችን ማፍራት ከማስቻሉ ባሻገር እንደ ሜም፣ ጥቅሳጥቅስ የመሳሰሉ ፈጣን መዝናኛና መማማሪያዎችን በማካተት እንደ ሪያሊቲ ሾው ሁሉ ሰው ሲዘለፍ ሲሸወድ ወዘተ ማሳየት ከመቻሉ ጋር ተይይዞ ከመዝናኛነትም አልፎ ወደ ሱስነት ደረጃ ከፍ በሚል ሁኔታ የዘመኑ የሰው ልጅ አንዱና ዋንኛ መገለጫ መሆን የሚችልበት ደረጃ በፍጥነት በመሸጋገር ላይ ነው።

እኔ ፌስቡክ አልጠቀምም የሚሉ ሰዎች በተለያየ መንገድ አልጠቀምም ቢሉም አጮልቀው የሚያዩ መሆናቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከናካቴው ምንም የሌሉበትም ቢሆኑ እንኳ ባንድ ወይም በሌላ መልኩ የፈስቡክ ተፅእኖ ሰለባ ናቸው። ሐሰተኛ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን ጨምሮ ጠቅላላው የፌስቡክ ተጠቃሚ በዓለም ከሁለት ቢሊዮን በላይ እንደሚሆኑ ልብ ካሉ ዘንዳ ከዓለም ሕዝብ ብዛት ነፍስ ያወቀው አንድ አራተኛው መጠቀሙን እግረ መንገድዎን ያስታውሱ።

የፈስቡክ ልክፍትና ሱሰኝነት እንዴት እንደሚጀምርና ካንዱ ወደ አንዱ እንዴት እንደሚጋባ የሥነ ልቦና ባለሙያዎች ገና እያጠኑት ያለ ሰፊ ምርምርና ጥናት የሚጠይቅ ዓለማችን በዚህ ዘመን የገጠማት የጋራ ማኅበራዊ ቀውስ ዋንኛ ምንጭ ነው።

የፀደይ አብዮት በመባል የሚታወቀው ሰደድ እሳት ቱኒዚያ ውስጥ በመሃመድ ቦአዚዚ ራስን ማቃጠል ሲነሣ ከአብዮቱ ጥንስስ ጀምሮ እስከ እንደ ሊቢያና ሶሪያን ሲያፈራርስ ፈስቡክ የአብዮቱ ዋንኛ ጦር መሣሪያ ነበር። በአሜሪካና የአውሮፓ ሃገራት የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ የነበረው ሚናም በዋዛ አይታይም። እዚህ ባገራችንም እነ ቄሮ፣ ፋኖ፣ ዘርማ ምን እንደሠሩበት የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው።

ፌስቡክ ለሰው ልጅ ይዞት የመጣው ገጸበረከት፦ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ፣ ለአጠቃቀም ምቹ መሆኑ፣ ፍጥነት ያለው የመልእክት ትልልፍ ዘዴ መሆን መቻሉ አንዱና ዋንኛው ነው። በተረፈ የዘመኑ ሰው ትግሥት የምትባለውን እንደ መቅበሩ በተለያየ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ምክንያት ቅንዝንዝ፣ ባለበት የማይረጋ፣ ችኩል ከመሆኑ ጋር የዚህ መተግበሪያ መፈጠር ሰኔና ሰኞ ሲገጣጠሙ ዓይነት ነገር ሆኗል።

በአጭሩ ሐተታ አይወድም ትውልዱና ጊዜው። ቁንፅል ነገር በልቶ ቁንፅል ነገር ይዞ ሩጫ (ፋስትፉድና ቪትስን እዚህ ላይ ልብ ይላሉ)። ምግባችን ፋስት ፉድ፣ ትምህርታችን ገለብ፣ ገለብ፣ ሥራችን ዝምብሎ ሩጫ ብቻ።

ፈስቡክ ጥሩ የሐሜት ሱስ መወጣጫም ነው። አንዱን ታዋቂ ወይም አንዷን ባለዝና ወርተራ ጠብቆ አፈር ድቤ ማብላት ቀላል ነው። ከዚህ በተረፈ የተለያየ ድብቅ ጥምን እና ነውርን ባደባባይ ማራመጃ መንገድም ነው ፌስቡክ። (ያው እንደሚታወቀው በሕፃናት ወሲብ ልክፍት የተለከፈ ወንጀለኛ፣ ከእንስሳት ጋር አጓጉል ድርጊት የሚፈጽም፣ የሰው ደም በማፍሰስ የሚረካ፣ ወዘተ እያለን ዘርዝረን አንጨርሰውም። የሰው ልጅ ድብቅ ሱስ ብዙ ነው ብለን እንለፈው)።

ዕብደት ማለት አንድ ተመሣሣይ ነገር እያደረጉ የተለየ ውጤት መጠበቅ መሆኑን ምሁራን ደጋግመው ተናግረውታል፤ እኛም ደጋግመን ሰምተነዋል። ምን ያክሎቻችን ምንም በዕለት ተዕለት ሕይወታችን ፋይዳ እንደሌለው እያወቅን እንጠቀምበታለን?

ዕብደት ብቻ አይደለም ያልሆንከውን መሆን ራሱ የዕብደት ጥግ መድረስ ምልክት ነው። ስንቱን ሐሳዊ ጋዜጠኛ፣ ሐሳዊ ሰብአዊ መብት ተሟጋች፣ ሐሳዊ ብሔርተኛ፣ ሐሳዊ አፍቃሪ፣ ሐሳዊ የአካባቢ አየር ተቆርቋሪ፣ ሐሳዊ ፓሊስ መርማሪ፣ ሐሳዊ ፖለቲከኛ፣ ሐሳዊ ታሪክ ጸሐፊ፣ ሐሳዊ ዐቃቤ ቅርስ፣ ሐሳዊ ታቦት አንጋሽ፣ ሐሳዊ ፓስተር ሰባኪ፣ ሐሳዊ አገር አቅኚ ሐሳዊ ወዘተ ሲሆን አይተናል። ምን ያላየነው አለ? እዚህ ዕብዶችና ወሬኞች፣ ሥራ ፈቶችና አስመሳዮች ባጥለቀለቁት የተበላሸ ምናብ መንደር ምን የሌለ አለ?

ቁርስ፣ ምሳና እራታችንን የምንበላበት ምግብ ቤት፣ አዲስ ልብስና ጫማ የምናስመርቅበት ቡቲክ፣ ቪዛ የምናስመታበት ኬላ፣ በግና ዶሮ ተራ፣ ላልታመምነውን እንዳንታመም መክረው የሚያሟርቱብን፣ ቀን መቁጠሪያ (ዛሬ እንትን ነው ነገ እንትና እንኳን አደረሳችሁ መባበያ)፣ ሚስትን ወይም ባልን እቅፍ አድርገው ፎቶ ተነሥተው መገለጫ (ፕሮፋይል) አድርገው ከመሬት ተነሥተው ትነካውና ትነካትና የሚመስል ዓይነት ዛቻ የምናሰማበትና የምናይበት፣ የልጆች ዕድገት የምንዘግብበት፣ ትኩስ የወሬ ምንጭ፣ ነጻ ጋዜጣ፣ ለቅሶ ቤት፣ ሰርግ ቤት፣ መቀጣጠሪያ፣ መጀናጀኚያ፣ ፍርድ ሸንጎ፣ ሕፃናት ማዋለጃ ክፍል፣ ሆስፒታል፣ የጽድቅና ኩነኔ መመዝገቢያ ባሕረመዝገብ ይመስል የተሳለሙትን ደብር፣ ያደረጉትን በጎ ምግባር የምንከትብበት፣ እቃ የምናሻሽጥበት፣ መፈንቅለ መንግሥት፣ የባለሥልጣን ሹም ሽር የምናደርግበት . . . ምን የማይባል፣ ምን የማይደረግ ነገር አለ እዚህ መንደር? ዓለምን እንደ መርካቶ ብናስባት ምናለሽ ተራ ነው በአጭሩ ፌስቡክ።

ፌስቡክ ዕልም ያለ የቀለጠው መንደር ሆኗል። እዚህ መንደር ያገር ሽማግሌ፣ የሃይማኖት አባት፣ ታላቅ ታናሽ፣ መሪ ተመሪ፣ ዳኛ፣ ፖሊስ የሚባል ነገር የለም። በራሱ ሕግ፣ በራሱ ቴምፖ፣ በራሱ ዜማ ስልት፣ በራሱ ሥርዓት ይመራል።

ለማንኛውም ወዳጄ ልቤ ከዚህ እንደ ስሙ ፌዝቡክ ነውና ብዙ አትጠብቅ። ፈስቡክ ዳቦ አይሆንም። ለወሬ የለው ፍሬ ለአበባ . . . ይባል የለ ከነተረቱ። ዋዛና ፈዛዛም ሲበዙ ቤት ሊያፈርሱ ይችላሉና ቆጠብ ማለቱ ለሁሉም ሳይበጅ አይቀርም። ዳይ ወደ ሥራ። ሥራ ባይኖር እንኳ አንበብ ነገ የምትመነዝረውን ሀብት ይሰጥሃል።
ከሣቴ ብርሃን ቡሩህ በዕለተ ማርያም የመጋቢቷ (2019)

Thursday, March 28, 2019

ከበሮና የሰው ልጅ ተመሳሌታዊ ዝምድና


ከበሮ በሥዕሉ ላይ እንደሚታየው ሦስት ዋንኛ ክፍሎች አሉት። አፉ ሰፋ የሚለው እና በዋንኛነት የሚመታው "ደባይ" ሲባል ሁለተኛው ጫፍ ጠበብ የሚለው እና ከጸናጽል ጋር እየተንሰላሰለ አልፎ አልፎ ምትን ለመጠበቅ ብቻ የሚነካው ወይም የሚመታው "ጥራይ" ይባላል። የከበሮውን አብዛኛውን ክፍል የሚሸፍነው ሆዱ ደግሞ "ከርሰ ከበሮ" ወይም "የድምፅ ሳጥን" በመባል ይታወቃል። 

የሰው ልጅም በአጠቃላይ ሲታይ በእነዚህ ሦስት የከበሮ ክፍሎች ተለይቶ ሊታይ ይችላል። ሕይወት ደግሞ እንደ ከበሮ መቺው። ደባይ የሚባለው ክፍል ታዋቂ ሰዎችን፣ ዝነኖችን፣ ፖለቲከኞችን፣ የሃይማኖት መሪዎችን፣ ባለልዩ ተሰጥዖ ሰዎችን ወዘተ ይወክላል። ምንም ያድርጉ ምን ጩኸታቸው ገኖ ቁልቁል እስከ ታች ይሰማል።ሦስተኛው ክፍል "ጥራይ" ደግሞ የለየለትን መናጢ ድሃ ይወክላል። ችግሩ ጥርስ ሲያወጣ፣ ጠኔው ሲበዛ ወደ ላይ ዘልቆ የላይኛውን ክፍል ደባዩን ቀልብ ይስባል። 

መሀለኛው ክፍል ማለትም ከርሰ ከበሮው ደግሞ በተለምዶ "አማካይ" የሚባለውን ወይም "መካከለኛውን ክፍል" ይወክላል። ከላይና ከታች የሚመጣውን ድምፅ ያስተጋባል። በሁለቱ ጠርዞች መካከል ያለውን ግንኙነት ወዲህና ወዲህ እያለ ድምፃቸውን በማቀባበል አንድ ወጥ ዜማ እንዲሰማ የበኩሉን ድርሻ ይወጣል።
ሕይወት በፈለገችው ምት እየደበደበች በነፍስ ወከፍና በጅምላ ከእያንዳንዱ የሰው ልጅ መስማት የምትፈልገውን ዜማ ትሰማለች። እያንዳንዱ ዘመንም የየራሱ ከበሮ ይኖረዋል። ለምሳሌ የግሪክ የዴሞክራሲ ዘመን፣ የሮማ ዘመን፣ የመስቀል ጦርነት፣ የተሃድሶ ዘመን፣ አንደኛ የዓለም ጦርነት፣ ሁለተኛ የዓለም ጦርነት፣ ቀዝቃዛው ጦርነት፣ ሽብርተኝነት፣ ግሎባይላይዜሽን እያለ ይቀጥላል።

ደባዮች ገነው ይጮኸሉ። ጥራዮችም በአቅማቸው የደባይን ምት ይቆጣጠራሉ። መሃል ሰፋሪዎችም መሃል ላይ ሆነው ሁለቱን ጫፍ ሲያዳምቁና ሲያደንቁ ይኖራሉ። ሁሉም ሕይወት የቀመረችላቸውን ዜማ እየተደለቁ አዚመው ያልፋሉ።

ከሣቴ ብርሃን ቡሩክ በዕለተ ገብሪኤል (2019 በራስ አቆጣጠር)
መነሻ ሐሳብ THE SUBTLE ART OF NOT GIVING A F*CK
Image may contain: food

Thursday, March 21, 2019

World Happiness Report 2019 የዓለም የደስተኛነት ሪፖርት 2019 እአአ

World Happiness Report 2019
የዓለም የደስተኛነት ሪፖርት 2019 እአአ
በደስተኛነት ደረጃ ከ156 አገሮች 134ኛ ብንሆንም የሚገርመው ግን ግብፅ፣ ኡጋንዳ፣ ህንድ፣ ማዳጋስካር፣ ሩዋንዳን ከመሳሰሉ አገሮች መሻላችን ደግሞ "እፎይ፣ ተመስገን !" የሚሉት ባህላችን ይሆን ያተረፈን? አሁንም ተመስገን በሉ ! ከኛም የከፋ አለና።
ከኛ በታች ያሉ አገሮች በጣም አንደኛ ከከፋት ከደቡብ ሱዳን ጀምሮ እስከ 134ኛ እኛ ድረስ ዝርዝሩ ከታች ወደላይ ይህን ይመስላል፦
156. South Sudan(2.853)
155. Central African Republic(3.083)
154. Afghanistan(3.203)
153. Tanzania(3.231)
152. Rwanda(3.334)
151. Yemen(3.380)
150. Malawi(3.410)
149. Syria(3.462)
148. Botswana(3.488)
147. Haiti(3.597)
146. Zimbabwe(3.663)
145. Burundi(3.775)
144. Lesotho(3.802)
143. Madagascar(3.933)
142. Comoros(3.973)
141. Liberia(3.975)
140. India(4.015)
139. Togo(4.085)
138. Zambia(4.107)
137. Egypt(4.166)
136. Uganda(4.189)
135. Swaziland(4.212)
በጣም ደስተኛዎቹ ደግሞ አነሆ፦
50. Romania(6.070)
49. Ecuador(6.028)
48. Cyprus(6.046)
47. Romania(6.070)
46. Argentina(6.086)
45. Kosovo(6.100)
44. Nicaragua(6.105)
43. Slovenia(6.118)
42. Colombia(6.125)
41. Lithuania(6.149)
40. Uzbekistan(6.174)
39. Poland(6.182)
38. Trinidad and Tobago(6.192)
37. Slovakia(6.198)
36. Bahrain(6.199)
35. Italy(6.223)
34. El Salvador(6.253)
33. Singapore(6.262)
32. Uruguay(6.293)
31. Brazil(6.300)
30. Panama(6.321)
29. Spain(6.354)
28. Qatar(6.374)
27. Saudi Arabia(6.375)
26. Guatemala(6.436)
25. Chile(6.444)
24. Taiwan Province of China(6.446)
23. France(6.592)
22. Mexico(6.595)
21. Malta(6.726)
20. United Arab Emirates(6.825)
19. Czech Republic(6.852)
18. United States(6.892)
17. Belgium(6.923)
16. Germany(6.985)
15. Ireland(7.021)
14. United Kingdom(7.054)
13. Luxembourg(7.090)
12. Israel(7.139)
11. Costa Rica(7.167)
10. Australia(7.228)
9. Austria(7.246)
8. Canada(7.278)
7. New Zealand(7.307)
6. Sweden(7.343)
5. Switzerland(7.480)
4. Netherlands(7.488)
3. Iceland(7.494)
2. Norway(7.554)
1. Denmark(7.600)
ሙሉ ዝርዝሩን ከዚህ በታች ማግኘት ይቻላል
https://s3.amazonaws.com/happine…/…/WHR19_Ch2A_Appendix1.pdf

Saturday, March 16, 2019

Brook Beyene: Arthur Rimbaud’s poems and works have been transla...

Brook Beyene: Arthur Rimbaud’s poems and works have been transla...: The French President Emmanuel Macron and the Ethiopian Prime Minister Dr. Abiy Ahmed leafing through the library edition of Passages. Passa...

Arthur Rimbaud’s poems and works have been translated by Brook Beyene

The French President Emmanuel Macron and the Ethiopian Prime Minister Dr. Abiy Ahmed leafing through the library edition of Passages. Passages (Bernard Dumerchez publishing house) is the French presidential gift to the Ethiopian Prime Minister. This is the first translation into Amharic of the French poet Arthur Rimbaud, who lived 10 years in Ethiopia and the Horn of Africa (1881-1891). Arthur Rimbaud’s poems and works have been translated by Brook Beyene, François Morand and Dr. Berhanu Abebe, and edited and prefaced by Alain Sancerni and Jean-Michel Le Dain. A co-edition has been published in Ethiopia with Shama Books and the French Embassy support.
On the same occasion, the library edition of Rimbaud selon Harar by Alain Sancerni and the artist Joël Leick (Bernard Dumerchez publishing house), has been given by the French President to the Ethiopian President Mrs Sahle Work Zewde.
N.O.E., 13/03/2019
Photo : le Monde, 12/03/2019

Image may contain: 4 people, including Zelalem Getahun, people smiling, suit