Friday, March 1, 2019

ወርሐ ግንቦት


ወርሐ ግንቦት
ግንቦት ፩
·         ፲፱፻፳፰ / - ኢጣልያ ንጉሥ ቪክቶርዮ ኢማኑኤል ሣልሣዊ፣ ኢትዮጵያ ሕዝብ እና ግዛት በኢጣልያ አስተዳደር ሥር የሚያደርግ አዋጅ አስንገረው፣ ይሄንኑ አዋጅ ለዓለም መንግሥታት እንዲሰራጭ አዘዙ። ኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥትነት ማዕርግ ከዚህ ዕለት ጀምሮ የእሳቸውና የወራሾቻቸው እንደሆነ፣ የኢትዮጵያም ሕዝብ እና ግዛት በእንደራሴ እንደሚታደደር በዚሁ አዋጅ ይፋ ተደርገ።
·         ፲፱፻፴፯ / - ኢጣልያ ንጉሥ ቪክቶርዮ ኢማኑኤል ሣልሣዊ፣ ከዙፋናቸው ወርደው ዘውዱ ወደንጉሥ ዳግማዊ ኡምቤርቶ ተዛወረ።
·         ፲፱፻፷፫ / የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ አቡነ ቴዎፍሎስ ስርዓተ ሲመት መንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናውኗል።
·         ፲፱፻፺፫ / - ጋና ርዕሰ ከተማ አክራ የእግር ኳስ ሜዳ በሚካሄድ ጨዋታ ላይ ተመልካች ሕዝብ በዳኛው ውሳኔ ባለመስማማቱ የተነሳውን ረብሻ ለማብረድ፣ ፖሊሶች የተኮሱት የጢስ ቦምብ ሕዝቡን የባሰውን ሲያተራምሰው በተከሰተው ትርምስና የሰው ግፊያ ፻፳፱ ሰዎች ተቸፍልቀው ህይወታቸውን አጡ።
·         ፲፰፻፵፬ /ራስ መኮንን  ልዕልት ተናኘወርቅ ሣህለ ሥላሴ እና ከደጃዝማች ወልደሚካኤል ወልደ መለኮት ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወለዱ።
ግንቦት ፪
·         ፲፱፻፹፮ / - ለሃያ ሰባት ዓመታት በእሥራት የቆዩት ኔልሰን ማንዴላ ለአገራቸው ደቡብ አፍሪቃ የመጀመሪያው ጥቁር ፕሬዚደንት በመሆን ቃለ-መሐላቸውን ፈጸሙ።
ግንቦት ፫
·         ፲፱፻፶፪ /ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጣልቃ ገቦች በአገሪቱ ጉዳይ ውስጥ እየገቡ አስቸግረዋል በሚል መነሻ ፈረንሳይን፤ አሜሪካን፤ ግብጽን፤ የሶቪዬት ሕብረትን፤ ብሪታኒያ እና ዩጎዝላቪያ የልዑካን አለቆች ሰብስበው አነጋገሩ። በማግሥቱ ይፋ የተደረገው ጽሑፋዊ ቃለ-ጉባኤ አምባሳደሮቹ የተጠሩትኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት በአፍሪቃ ቀንድ አካባቢ ጉዳዮች ላይ የባዕዳንን ጣልቃ ገብነት በብርቱ እንደሚቃወም እና ኢትዮጵያ ግዛትና ሉዐላዊነት ላይ የሚሰነዘሩትን ማናቸውንም እርምጃዎች ለመከላከል ቆራጥ መሆኑን እንዲገነዘቡ ነው።ይላል።
·         ፲፱፻፷፭ /ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ግብጽ ፕሬዚደንት ሳዳት ጋር ለውይይት ወደካይሮ ሲጓዙ፣ እግረ መንገዳቸውን ካርቱም ላይ አርፈው ከፕሬዚደንት ኒሜሪ ጋር ተለወያዩ።
ግንቦት ፬
·         ፲፱፻፶፪ / - ዮርዳኖስ ንጉሥ ሁሴን ለአራት ቀን ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ።
ግንቦት ፭
·         ፲፱፻፷፫ / - በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) ተማሪዎች አድማ መቱ።
·         ፲፱፻፵፱ / - ልዑል መኮንን ኃይለ ሥላሴ መስፍነ ሐረር ናዝሬት መንገድ ሞጆ አካባቢ ላይ በመኪና አደጋ በሞት ተለዩ።
ግንቦት ፮
*********
ግንቦት ፯
*********
ግንቦት ፰
·         ፲፱፻፰፩ ዓ/ም - በኮነሬል መንግሥቱ ኃይለማርያም ላይ የመፈንቀለ መንግሥት ሙከራ ተደረገ።
·         ፲፱፻፴ /ኢትዮጵያዊው የሙዚቃ ምሑር፤ አስተማሪ፤ ደራሲ እና የቅዱስ ያሬድ የሙዚቃ ትምሕርት ቤት መሥራች ዶክቶር አሸናፊ ከበደ በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ተወለዱ።
·         ፲፰፻፷ / - ዓፄ ቴዎድሮስ ሚስት እና ልዑል ዓለማየሁ እናት፤ እቴጌ ጥሩነሽ በዚህ ዕለት አረፉ።
·         ፲፱፻፺ /ኢትዮጵያዊው የሙዚቃ ምሑር፤ አስተማሪ፤ ደራሲ እና የቅዱስ ያሬድ የሙዚቃ ትምሕርት ቤት መሥራች ዶክቶር አሸናፊ ከበደ በዛሬው ዕለት በተወለዱ በስልሳ ዓመታቸው አረፉ።
ግንቦት ፱
·         ፲፱፻፷፫ / - አዲስ አበባ ጄኔራል ዊንጌት ትምህርት ቤት የተመሠረተበትን ፳፭ኛ ዓመት በዓል ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በተገኙበት አከበረ።
ግንቦት ፲
*********
ግንቦት ፲፩
·         ፲፱፻፶፪ / - ኤርትራ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያጸደቀውን ሕገ-መንግሥቱን በመለወጥ አገሪቱን ኤርትራ መንግሥትወደ ኤርትራ አስተዳደርበመለወጥ ወደፊት ሙሉ ኢትዮጵያ አካል ለማድረግ የሚስችላትን ውሳኔ አጸደቀ።
ግንቦት ፲፪
·         ፲፬፻፹፮ /ዓፄ እስክንድር በነገሡ በ፲፮ ዓመታቸው አረፉና በደብረ ወርቅ ተቀበሩ። ሥልጣነ መንግሥታቸውም ወደ ዓመቱ ልጃቸው ዓምደ ጽዮን ሣልሳዊ ተዘዋወረ። ሆኖም ዓምደ ጽዮን በነገሡ በ፯ ወራቸው ድንገት ስለሞቱ አልጋው ወደ አባታቸው ወንድም አጼ ናዖድ ተላልፏል።
·         ፲፯፻፲፫ /አፄ ዳዊት ሣልሳዊ በዚህ ዕለት አረፉ።
ግንቦት ፲፫
·         ፲፱፻፳፱ / - የካቲት ፲፪ ቀን አዲስ አበባ ላይ ግራዚያኒ ላይ የተወረወረውን ቦምብ ምክንያት በማድረግ ፋሺስቶች ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገብተው ፫፻፳ መነኮሳትን በግፍ ጨፈጨፉ፤ ገዳሙንም አቃጠሉ።
·         ፲፱፻፷፮ / - ኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት አሩሲ ጠቅላይ ግዛት (አሁን አርሲ) እንደራሴ ሆነው የተሾሙትን አቶ ተስፋ ቡሸን የጠቅላይ ግዛቱ ሕዝብ አባሮ አስወጣቸው።
·         ፲፱፻፹፫ / - የኢሕዲሪ (ኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ) ፕሬዚዳንትና የኢሠፓ (ኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ) ዋና ጸሐፊ የነበሩት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም አገር ጥለው በመኮብለል ዚምባብዌ ገቡ።
·         ፲፱፻፳፱ / - ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም በዚህ ዕለት አዲስ አበባ ተወለዱ።
ግንቦት ፲፬
*********
ግንቦት ፲፭
*********
ግንቦት ፲፮
·         ፲፱፻፹፫ /ኤርትራ ኢትዮጵያ ተገንጥላ ራሷን የቻለች ሉዐላዊ አገር ሆነች።
ግንቦት ፲፯
·         የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የተመሠረተበትን ዕለት በማስታወስ ይህ ዕለት በመላው አፍሪቃ አኅጉር የአፍሪቃ ቀን ተብሎ ይከበራል።
·         ፲፱፻፶፭ / - የ፴፪ ነጻ አፍሪቃ አገራት መሪዎች አዲስ አበባ ላይ ተሰብስበው የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት መሠረቱ።
·         ፲፱፻፷፫ / - አዲስ አበባ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ፤ በከተማው አውቶብሶች እና ንብረት ላይ ጉዳት አደረሱ። በዚህም ምክንያት አሥር ሁለተኛ ደረጃ ትምሕርት ቤቶች ተዘጉ።
ግንቦት ፲፰
·         ፲፯፻፲፫ / - ከወህኒ በወረዱ በሁለተኛው ቀን አፄ አድያም ሰገድ ኢያሱ ልጅ አፄ በካፋ ጎንደር ላይ በጳጳሱ አባ ክርስቶዶሉ እና እጨጌ ተክለ ሃይማኖት ተቀብተው ነገሡ።
·         ፲፱፻፶፪ / - ሶቪዬት ሕብረት የኢንዱስትሪ እና የቴክኒክ ምርቶች አውደ ርዕይ አዲስ አበባ ላይ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተመርቆ ተከፈተ።
·         ፲፱፻፷፭ /የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት አሥረኛው የመሪዎች ስብሰባ አዲስ አበባ ተከፈተ።
ግንቦት ፲፱
·         ፲፱፻፷፮ / - ኤርትራ ነጻ አውጪ ግንባር አባላት ጊንዳ ውስጥ በሉተራን ሚሲዮን ሆስፒታል ውስጥ የሚሠራ ዶክቶርን የመጥለፍ ሙከራ ሲያደርጉ አንዲት አስታማሚ (ነርስ) ተገደለች።
·         ፲፱፻፷፮ / - የቴሌኮሙኒኬሽን ሠራተኞች በአድማ ሥራቸውን አቆሙ።
ግንቦት ፳
·         ፲፱፻፷፮ / - የጠቅላይ ሚኒስትር እንዳልካቸው መኮንን መንግሥት የሚኒስትሮችን ለውጥ ይፋ አደረገ። ከነዚህም አንዱ የአገር ግዛት ሚኒስትር የነበሩትን ደጃዝማች ዘውዴ ገብረ ሥላሴ ወደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መዛወር ያካትታል።
·         ፲፱፻፹፫ /ኢሕአዴግ በዘመቻ ወጋገን አዲስ አበባ ተቆጣጠረ። አቶ መለስ ዜናዊ የሽግግሩ መንግሥት ፕሬዚዳንት ሆኑ።
ግንቦት ፳፩
·         ፲፰፻፸ / አፄ ዮሐንስ እና ሸዋ ንጉሥ ምኒልክ በተገኙበት ወሎ ቦሩ ሜዳ ላይ የተካሄደው የሃይማኖት ክርክር እልባት አገኘ፡፡
ግንቦት ፳፪
·         ፲፱፻፷፮ / - ኢትዮጵያ ሕዝባዊ አመጽ ቆስቋሽነት የተሠየመው የሙስና እና የሥልጣን በደል መርማሪ ሸንጎ ሥራውን የሚመራበት ሕግ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸደቀ።
ግንቦት ፳፫
·         ፲፱፻፯ /ልጅ ኢያሱ አባታቸውን ራስ ሚካኤል ደሴ ላይ ንጉሠ ወሎ  ትግሬ ብለው አነገሧቸው።
ግንቦት ፳፬
·         ፲፱፻፶፫ / - በ፳ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በትልቅነቱ ኢትዮጵያ ታሪክ አቻ የሌለው ሪክተርሚዛን ስድስት ነጥብ ሰባት ያስመዘገበ የመሬት እንቅጥቅጥ ተከስቶ የማጀቴን ከተማ ሲደመስስ፣ በጎረቤቷ ካራቆሬ ደግሞ ከመቶ እጅ አርባ አምሥቱ መኖሪያ ቤቶች ወድመዋል። ከካራቆሬ በስተሰሜን የሚያልፈው ዋናው አዲስ አበባ አስመራ መንገድ እና ድልድዮችም እንቅጥቅጡ ባስከተለው የድንጋይ ናዳ ወደ አሥራ ሰባት ኪሎ ሜትር ርዝመት ላይ አደጋ ደረሰ
ግንቦት ፳፭
·         ፲፯፻፹፰ / - አመድ ከሰማይ ዘነበ።
·         ፲፱፻፳፩ / - ግብጽ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የመጀመሪያዎቹን አራት ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት (አቡነ አብርሓም - ጎንደር እና ጎጃም አቡነ ይስሐቅ - ትግሬ እና የስሜን፤ አቡነ ጴጥሮስ ወሎ እና የላስታ፤ አቡነ ሚካኤል - ኢሉባቡር እና የምዕራብ ኢትዮጵያ) ከግብጻዊው ሊቀ ጳጳሳት (አቡነ ቄርሎስ)ጋር ካይሮ ላይ ተቀብተው ተሾሙ።
ግንቦት ፳፮
·         ፲፯፻፷፭ / - ዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ።
ግንቦት ፳፯
·         ፲፱፻፷፭ / - በመከላከያ ሚኒስትር ጄኔራል ሊዩቢቺክ የሚመራ ዩጎዝላቪያ ወታደራዊ ቡድን ኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጋር አዲስ አበባ ላይ ያካሄደውን የአራት ቀን ውይይት ጀመረ።
ግንቦት ፳፰
·         ፲፱፻፹፫ / - በአዲስ አበባ ከተማ በቆሎ ሰፈር አካባቢ የሚገኝ ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ በተነሣ ፍንዳታ በርካታ ሕይወት አለፈ፤ ብዙ ቤቶችና ንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ።
ግንቦት ፳፱
*********
ግንቦት ፴
·         ፲፱፻፴፫ /አዲስ ዘመን በሚለው መጠሪያ የሚታወቀው ብሔራዊ ጋዜጣ በይፋ ሥራ ጀመረ። የጋዜጣው ሥያሜ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ / በድል አድራጊነት ሲገቡ «ይህ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የአዲስ ዘመን መጀመሪያ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል።
·         ፭፻፴ / - ኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዓፄ ካሌብ አረፉ።

No comments:

Post a Comment