ሐበሻ
ከነካኩት እንጂ ካልነኩት አይነካም
ሐበሻ ራሱን እንጂ የሰው ዘር አይጠላም
ልብ እና ኩላሊት እንደ ፊት አይታይም
አይቻልም እንጂ ቢቻል ነበር መልካም
የፊጢኝ ታስሮ በውቅያኖስ ዋና
በፋኖስ መለወጥ የፀሐይን ፋና
የነብርን ጅራት ለቆ ሩጫ
አህያ ሰፈር ገብቶ እርግጫ
ጅብን አቅፎ እንቅልፍ
እባብን አምኖ ማሳለፍ
ሐበሻን ሐበሻ በሾኬ ካልጠለፈ
ወንድሙ ላይ ታርጋ ካልለጠፈ
ቃሉን አጥፎ መንገድ ካላጠፈ
አጥፎም በሽብር ደም ካልተራጨ
ሴራ ሸርቦ እንደ ነጠላው ካልቋጨ
ጎረቤቱ በበላው ሆዱን ካልታመመ
እንዲያሽረው ኮሶ በኮሶ ካልታከመ
እንዳይበለጥ በዘመዱ ተንኮል ካልሸረበ
መርፌ ሰክቶ በግድግዳ ጠንቋይ ካልቀለበ
ባላንጣ ሆኖ መሳይ ባልንጀራ
ለታይታ ፍቅሩ መዐድ ካልተጋራ
ግራ እየገባው ካላጋባ ግራ
ዐረብን አርጎ ዲኑ
በራሱ መጨከኑ
ፈረንጅ አርጎ መልአኩ
የጠፋበት ሚዛን ልኩ
ለቀብር ከሰነፈ ጉልበቱ
በሞተ ከጨከነ አንጀቱ
ምቀኛ ካሳጣው ጸሎቱ
ጥሬ ቢያጣ ካልቆረጠመ ጥራጥሬ
ታሪኩን ካላወጋ ተቀምጦ በወሬ
እና ይኼን ሁሉ ዐውቀው እንዳይርቁት
ክፋቱን ብቻ ዐይተው እንዳይጠሉት
ገዳም ገብቶ መላክ ያናግራል
ሰማይ ቤት በምድር ያደናግራል
የፈጣሪ ስም ጠርቶ ወኔህን ይሰልባል
ችግር ፈጥሮ ራሱ ባካል
ለነፍስ ምስጢር ይፈታል
ምሥራቅ ሲሉት ምዕራብ
ሰሜን ሲሉት ደቡብ
ያለም እንደርቢ አዋኪ ሸዋኪ
እውነትን አንቆ እምነትን ሰባኪ
ሐበሻን ዐውቃለሁ ማለት ዘበት
ብልቃጥ ያልገባ መርዝና መዳኒት
ኋላ ሲሉት ከፊት ከፊት ሲሉት ኋላ
ታንገት ተሽጦ በፍቅር አንገት የሚቀላ
እንብላ ብሎ በአንደበቱ ስተህ ብትበላ
በሆድህ ስም ሰጥቶ አፈር ድሜ የሚያስበላ
ይኼን ዘመን የማይፈታው እንቆቅልሽ
ተዉት ባለበት ሳይነጋ እንዳይመሽ
አይነኬን ነክተን ቀልባችን እንዳይሸሽ
ተሰፍርን ዝም አልን በሥዩመ እዝጊ ዘሐበሽ
ጉያችን ጣፍጦ ገብቶ ሲያቀረናን እንደ አብሽ
ዓሣን ካልበሉት በብላት
ሐበሻን ካላወቁ በሥርዓት
ሕይወትም ይሆናል ለግጥ ዕውቀትም ሁሉ ከንቱ
ሐበሻን ልብ ብለው ካላዩ ከሥር መሠረቱ
ሕይወትም ይሆናል ለግጥ ዕውቀትም ሁሉ ከንቱ
ሐበሻን ልብ ብለው ካዩ ከጥንት ከጠዋቱ
ያው ዞሮ ዞሮ ድንቅነሽ ናት እናቱ
ከነካኩት እንጂ ካልነኩት አይነካም
ሐበሻ ራሱን እንጂ የሰው ዘር አይጠላም
ልብ እና ኩላሊት እንደ ፊት አይታይም
አይቻልም እንጂ ቢቻል ነበር መልካም
የፊጢኝ ታስሮ በውቅያኖስ ዋና
በፋኖስ መለወጥ የፀሐይን ፋና
የነብርን ጅራት ለቆ ሩጫ
አህያ ሰፈር ገብቶ እርግጫ
ጅብን አቅፎ እንቅልፍ
እባብን አምኖ ማሳለፍ
ሐበሻን ሐበሻ በሾኬ ካልጠለፈ
ወንድሙ ላይ ታርጋ ካልለጠፈ
ቃሉን አጥፎ መንገድ ካላጠፈ
አጥፎም በሽብር ደም ካልተራጨ
ሴራ ሸርቦ እንደ ነጠላው ካልቋጨ
ጎረቤቱ በበላው ሆዱን ካልታመመ
እንዲያሽረው ኮሶ በኮሶ ካልታከመ
እንዳይበለጥ በዘመዱ ተንኮል ካልሸረበ
መርፌ ሰክቶ በግድግዳ ጠንቋይ ካልቀለበ
ባላንጣ ሆኖ መሳይ ባልንጀራ
ለታይታ ፍቅሩ መዐድ ካልተጋራ
ግራ እየገባው ካላጋባ ግራ
ዐረብን አርጎ ዲኑ
በራሱ መጨከኑ
ፈረንጅ አርጎ መልአኩ
የጠፋበት ሚዛን ልኩ
ለቀብር ከሰነፈ ጉልበቱ
በሞተ ከጨከነ አንጀቱ
ምቀኛ ካሳጣው ጸሎቱ
ጥሬ ቢያጣ ካልቆረጠመ ጥራጥሬ
ታሪኩን ካላወጋ ተቀምጦ በወሬ
እና ይኼን ሁሉ ዐውቀው እንዳይርቁት
ክፋቱን ብቻ ዐይተው እንዳይጠሉት
ገዳም ገብቶ መላክ ያናግራል
ሰማይ ቤት በምድር ያደናግራል
የፈጣሪ ስም ጠርቶ ወኔህን ይሰልባል
ችግር ፈጥሮ ራሱ ባካል
ለነፍስ ምስጢር ይፈታል
ምሥራቅ ሲሉት ምዕራብ
ሰሜን ሲሉት ደቡብ
ያለም እንደርቢ አዋኪ ሸዋኪ
እውነትን አንቆ እምነትን ሰባኪ
ሐበሻን ዐውቃለሁ ማለት ዘበት
ብልቃጥ ያልገባ መርዝና መዳኒት
ኋላ ሲሉት ከፊት ከፊት ሲሉት ኋላ
ታንገት ተሽጦ በፍቅር አንገት የሚቀላ
እንብላ ብሎ በአንደበቱ ስተህ ብትበላ
በሆድህ ስም ሰጥቶ አፈር ድሜ የሚያስበላ
ይኼን ዘመን የማይፈታው እንቆቅልሽ
ተዉት ባለበት ሳይነጋ እንዳይመሽ
አይነኬን ነክተን ቀልባችን እንዳይሸሽ
ተሰፍርን ዝም አልን በሥዩመ እዝጊ ዘሐበሽ
ጉያችን ጣፍጦ ገብቶ ሲያቀረናን እንደ አብሽ
ዓሣን ካልበሉት በብላት
ሐበሻን ካላወቁ በሥርዓት
ሕይወትም ይሆናል ለግጥ ዕውቀትም ሁሉ ከንቱ
ሐበሻን ልብ ብለው ካላዩ ከሥር መሠረቱ
ሕይወትም ይሆናል ለግጥ ዕውቀትም ሁሉ ከንቱ
ሐበሻን ልብ ብለው ካዩ ከጥንት ከጠዋቱ
ያው ዞሮ ዞሮ ድንቅነሽ ናት እናቱ
የቅዱስ መርቆርዮስ ለታ ትሳስ 2018
የሐበሻ ስምንት ዐመት ኋላ መቅረት፣
አለው አንዳች ነገር አለው አንዳች ብላት
የሐበሻ ስምንት ዐመት ኋላ መቅረት፣
አለው አንዳች ነገር አለው አንዳች ብላት
ብሩክ በ.
No comments:
Post a Comment