አይ ያንቺ ነገር
የባሕር ላይ ኩበት
ወይ አይፈረፈር
ወይ ሰምጦ 'ማይተዉት
ወዲህና ወዲያ እየተላጋ
ሌት ተቀን ከንቱ እያተጋ
መዋተት ብቻ ምንም ላያተርፉ
ከከንቱ አብረው እየተንሳፈፉ
ያንቺ ነገር የባሕር ላይ ኩበት
እያየን፣ እያወቅን ዕድሜ ፈጀንበት
በወርሐ ሽሞኒም ዕለት 27፣ 2016 አዲስ አበባ ተጻፈ
መታሰቢየነቱ ለጋሽ ፀጋዬ በዳሶ (ሐሳቡን ለሰጡኝ)
No comments:
Post a Comment