Friday, October 21, 2016

የባህር ላይ ኩበት


አይ ያንቺ ነገር
የባሕር ላይ ኩበት
ወይ አይፈረፈር
ወይ ሰምጦ 'ማይተዉት
ወዲህና ወዲያ እየተላጋ
ሌት ተቀን ከንቱ እያተጋ
መዋተት ብቻ ምንም ላያተርፉ
ከከንቱ አብረው እየተንሳፈፉ
ያንቺ ነገር የባሕር ላይ ኩበት
እያየን፣ እያወቅን ዕድሜ ፈጀንበት

በወርሐ ሽሞኒም ዕለት 27፣ 2016 አዲስ አበባ ተጻፈ
መታሰቢየነቱ ለጋሽ ፀጋዬ በዳሶ (ሐሳቡን ለሰጡኝ)

No comments:

Post a Comment