የጠፋ ልብ
አፍቅሬሽ ነበረ
እውነት ያን ሰሞን
ወድጄሽ ነበረ
አምና ያኔ ልክ እንደ ዘንድሮ
አልገባሽም ግን አንቺ
ከልቤ እንደሆን
አሁን ግን . . . አሁን ግን
ልቤም ተስፋ ቆርጦ
በሮ ሄዷል የለም ከቦታው
ወጥቷል ከሰገባው
ላይመለስ ላይገባ ከስፍራው
እና አሁን ከረፈደ ጊዜው
እንኳንስ ላንቺ፤ ለኔም
እንኳንስ ላንቺ፤ ለኔም
ጠፍቶኛል አድራሻው
በወርሐ ሽሞኒም የፈረንጆቹ ዕለት 21
2016 አዲስ አበባ ተጻፈ
No comments:
Post a Comment