ነውር የሆኑ ወይም ጥንቃቄ
የሚያስፈልጋቸው ነገሮች
1.
ግራ መዳፍን ካሳከከህ ገንዘብ
ታገኛለህ፤ ቀኙን ከሆነ ደግሞ ገንዘብ ታወጣለህ።
2.
ቡና ወይም ሻይ ስትጠጣ
ስኳር ከግራ ወደ ቀኝ የምታማስል ሰው ከሆንክ ገንዘብ አጥፊ፣ በታኝ ነህ በተቃራኒው የምታማስል ከሆነ ማለትም ከቀኝ ወደ ግራ
(ወደ ውስጥ ወይም ወደ ራስህ አቅጣጫ) የምታማስል ከሆነ ገንዘብ ሰብሳቢ፣ ቆጣቢ፣ ወይም አሳዳጅ ነህ።
3.
ሙቀጫ ላይ መቀመጥ አጎትን
ወይም የቅርብ ዘመድን ይገላል።
4.
ማታ ቤት አይጠረግም።
አለበለዚያ የቤቱ ሲሳይ ተጠርጎ ይሄዳል።
5.
ማታ ማታ ጥፍር አይቆረጥም፣
የሚወዱት የቅርብ ሰው ይሞታል።
6.
ሳሙና መቀባበል የአንዱን
ሲሳይ ወይም መጥፎ ዕድል ከአንዱ ወደ አንዱ እንዲተላለፍ ያደርጋል።
7.
እንጀራ፣ ልጅ፣ ከብት
ብዛታቸው ለሰው አይነገርም። ብዛቱን ቆጥሮ የተናገረ መዓት ይመጣበታል።
8.
የልደታ ቀን ቤቱ ሙሉ
የሆነ ወሩን ሙሉ ቤቱ ሙሉ ይሆናል። ልደታ ቀን ወጪ የሚያወጣ ሰው ወሩን ሙሉ ወጪ ሲያወጣ ይከርማል።
9.
ዘነዘና መቀባበል መጥፎ
ምልክት ነው። ያጨካክናል።
10.
ከመሸ ለጎረቤት ጨው፣
በርበሬ፣ ክብሪት ማዋስ መጥፎ ነው። ለዚያኛው ቤት እሳት እንደ መስደድ ይቆጠራል።
11.
ቢላ በስለቱ ለሰው ማቀበል
መጥፎ ነው። ከተሳሳትክ በአፍንጫው ወዲያው መሬት መውጋት አለብህ።
12.
እርጉዝ ሴት ድንጋይ
ላይ መቀመጥ የለባትም። የምትወልደው ሰው አይሆንም።
13.
ቃሪያን ሁለት ቦታ ከፍሎ
ተካፍሎ መብላት ነውር ነው፤ ያቆራርጣል።
የጥሩ ዕድል ምልክቶች
ወይም የመጥፎ ነገር ምልኪዎች
1.
ቤት ውስጥ አይጥ ከገባ
ምቀኛ ሰው ቤትህን አይቶታል ማለት ነው።
2.
ውሻ ሌሊት ካላዘነ ሰፈር
ውስጥ የሆነ ሰው ይሞታል።
3.
ቡና ሲቀዳ አረፋ ከሠራ
የተቀዳለት ሰው ሲሳይ አለው፣ ቀኑ የተቃና ነው፣ ገንዘብ ያገኛል ማለት ነው።
4.
ዓይን ቆብ እርግብግብ
ካለ የጠፋ ዘመድ፣ ወዳጅ፣ ወይም ሩቅ አገር ያለን ሰው በቅርቡ ታያለህ።
5.
ቤት ውስጥ የጫማ ሶል
ተገልብጦ በሶሉ በኩል መሬት ላይ መጣል የለበትም። መጥፎ ነገር በዚያ ቤት ውስጥ ያጋጥማል።