የካቲት ፩
- ፫፻፹፮ዓ/ም - በክርስትና ሃይማኖት የተከሰቱትን ተቃራኒ ትምህርቶች በጉባኤ ለመወሰን የቁስጥንጥንያው ንጉሥ ቀዳማዊ ቴዎዶስዮስ ባስተላለፈው ጥሪ መሠርተ ፩፻፶ ሊቃውንት፣ ኤጲስ ቆጶሳት በቁስጥንጥንያ ጉባኤ ተሳትፈው መቅዶንዮስን፤ አፖሊናሪዮስን እና ሌሎችን መናፍቃንን አወገዙ።
የካቲት ፪
- ፲፱፻፴ዓ/ም - ቡልጋ ጨመሪ ላይ እነ ደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህ እና ሌሎችም አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ገጥመው ትልቅ ውጊያ ተደረገ።
የካቲት ፫
- ፲፯፻፰ዓ/ም - በእስራት ላይ የነበሩት የ ፳፩ ዓመቱ ጎልማሳና የንጉሥ ኢያሱ አድያም ሰገድ ልጅ ዳግማዊ ዓፄ ዳዊት እንደነገሡ አዋጅ ተነገረ።
- ፲፰፻፵፯ዓ/ም - ደጃዝማች ካሳ (ዓፄ ቴዎድሮስ)ና ደጃዝማች ውቤ ቧሂት ላይ ድንኳን ተክለው ተገናኙ። ደጃዝማች ካሳም የእንግሊዙን ሊቀ መኳስ ዮሐንስን (John Bell)በመንጥር አይተህ ንገረኝ አሉት። የሸማ ድንኳን ባየ ጊዜ ነገራቸው። ደጃዝማች ካሳም «አያሳድረኝ አላሳድረውም» ብለው ተናገሩ። ያንጊዜውንም ተነሣ አሉ። ባሰለፉትም ጊዜ እንዴህ ብለው በፍከራ ትንቢት ተናገሩ። «እንኳን ይህን ቁርጥማታም ወሎን፣ መትቼ የሻዋውን ንጉሥ እይዘዋለሁ። ስሜን ስሜን እንግርሀለሁ ያልሁህ ወታደር ስሜም ቴዎድሮስ ነው» አሉ። አስቀድሞ ገና በንጉሥ አምላክ በል። ስሜን ስሜን እነግርሀለሁ ብለው ነበርና። ያንጊዜውን እንዴህ አሉ። «ወታደር አይዞህ አትፍራ። የውቤ ነፍጥ የውቤ ነፍጥ ቢልህ የተለጎመው ጨርቅና ባሩድ ነው። አይነካህም» አሉት። እኔ የክርስቶስ በርያ ሁሉንም አሳይሀለሁ ወታደር ባሉ ጊዜ ሰልፍ ገጠመ። ደጃች ውቤም ተያዙ።
የካቲት ፬
- ፲፱፻፱ዓ/ም - ንግሥት ዘውዲቱ፣ "ግርማዊት ዘውዲቱ፣ ንግሥተ ነገሥት ዘኢትዮጵያ" ተብለው በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በሊቀ ጳጳሱ በአቡነ ማቴዎስ እጅ ቅብዐ መንግስት ተቀብተው የንጉሠ ነገሥቱን ዘውድ ጫኑ።
- ፲፱፻፶፭ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት በኢራቅ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ለተተካው የኮሎኔል አብዱል ሳላም አሪፍ መንግሥት ሕጋዊ ዕውቀት መስጠቱን አስታወቀ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - በ ደብረ ዘይት፣ ድሬ ዳዋ እና አስመራ የተመደቡ የዓየር ኃይል ባልደረቦች በአብዮት ፍንዳታ ተሳታፊ በመሆን አድማቸውን ጀመሩ።
- ፲፱፻፹፪ዓ/ም - በደቡብ አፍሪቃ የዘረኛ (አፓርታይድ) ሥርዓት ለ፳፯ ዓመታት በእስራት የቆዩት ኔልሰን ማንዴላ ተፈቱ።
- ፲፱፻፲ዓ/ም - «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ » በሚል ቅፅል ስም የሚታወቁት የዳግማዊ ምኒልክ ባለቤት፣ እቴጌ ጣይቱ ብጡል አረፉ። ሥርዓተ ቀብራቸውም በእንጦጦ መንበረ ፀሓይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተፈጸመ። በኋላ ግን አጽማቸው ተነስቶ ንግሥት ነገሥታት ዘውዲቱ ለአባታቸው ዳግማዊ ምኒልክ አጽም ማሣረፊያ በተሠራው የታዕካ ነገሥት በዓታ ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል።
- ፲፮፻፹፭ዓ/ም - ንጉሡ አጼ ኢያሱ ከጳጳሱ አባ ሲኖዳ እና እጨጌ ዮሐንስ ጋር አክሱም እንዳሉ ሙራድ የተባለ ታላቅ ግብጻዊ ነጋዴ በሕንድ ውቅያኖስ መጥቶ ከሆላንድ ንጉሥ ያመጣውን ሰላምታ እና ደብዳቤ አቀረበ።
- ፲፯፻፰ዓ/ም - ማክሰኞ ዕለት የአጼ ኢያሱ አድያም ሰገድ ልጅ ንጉሥ ዳዊት፣ አጼ ዳዊት አድባር ሰገድ ተብለው ዘውድ ጭነው ነገሡ።
- ፲፰፻፵፯ዓ/ም - ደጃዝማች ካሳ ኃይሉ ደረስጌ ማርያም ላይ አቡነ ሰላማ ቀብተዋቸው ዘውድ ጭነው ዓፄ ቴዎድሮስ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተባሉ።
- ፲፭፻፶፭ዓ/ም - የ ፲፪ ዓመቱ ልጅ ማር (ጌታ) ሠርፀ ድንግል፣ አባታቸው አጼ ሚናስ ሲሞቱ በስመ መንግሥት መለክ ሰገድ ተብለው ነገሡ። አጼ ሠርፀ ድንግል የመንግሥት ሥራቸውን የሚሠሩት በእናታቸው በእቴጌ አድማስ ሰገድ ሥሉስ ኃይላ አማካይነት ነበር።
- ፲፭፻፶፭ዓ/ም ኢትዮጵያን ከአራት ዓመታት በንጉሥነት የመሯት አፄ ሚናስ (ስመ መንግሥት፣ ቀዳማዊ አድማስ ሰገድ) በዕለተ እሑድ አረፉ፡፡ አጼ ሚናስ የአጼ ገላውዴዎስ ወንድምና የአጼ ልብነ ድንግል ልጅ ነበሩ።
- ፲፱፻፶፫ዓ/ም የቀድሞዋ ኮንጎ ሊዮፖልድቪል (የአሁኗ የኮንጎ ሪፑብሊክ) የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ፓትሪስ ሉሙምባ መገደላቸው ይፋ ተደረገ።
- ፲፱፻፷፭ዓ/ም የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የመከላከያ ንዑስ ሸንጎ አባላት አዲስ አበባ ላይ ስብሰባቸውን ጀመሩ።
- ፲፭፻፴፬ዓ/ም - ኢትዮጵያን ሊረዳ የመጣው የቡርቱጋል ሠራዊት ጦር መሪ ዶም ክሪስታቮ ደጋማ በአህመድ ግራኝሠራዊት ላይ አምባ ስንኢት በሚባል ሥፍራ ዘመተ።
- ፲፰፻፺፰ዓ/ም - ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ የመጀመሪያውን የአቢሲኒያ ባንክ በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ላይ መርቀው ከፈቱ።ከምርቃቱ ሥርዓትም በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ በቁጠባ ደብተራቸው የጠገራ ብር በባንኩ በማስቀመጥ የአዲሱ ባንክ ሁለተኛ ደምበኛ ኾኑ። የመጀመሪያው ደምበኛ በወቅቱ ለጉብኝት አዲስ አበባ ገብቶ የነበረው እንግሊዛዊው አርኖልድ ሄንሪ ሳቬጅ ላንዶር (Arnold Henry Savage Landor) ነበር።
- ፲፱፻፳፯ዓ/ም - በሆለታ ገነት፣ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ስም የጦር ተማሪ ቤት ተከፈተ።
- ፲፱፻፶፬ዓ/ም - እቴጌ መነን አስፋው በዚህ ዕለት በተወለዱ ፸፫ ዓመታቸው አረፉ።
- ፲፱፻፶፫ዓ/ም - በአዲስ አበባ የብሥራተ ወንጌል ራዲዮ ጣቢያን ለመትከል በኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት እና የሉተራውያን የዓለም ኅብረት መሃል የውል ስምምነት ተፈረመ።
- ፲፰፻፹፱ዓ/ም - ራስ አሉላ እንግዳ(አባ ነጋ) በዚህ ዕለት አረፉ።
- ፲፯፻፴፮ዓ/ም - ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ (ስመ መንግሥት፤ ብርሃን ሰገድ) ከጳጳሱ አባ ዮሐንስ እና ከ እጨጌ ኤውስጣቴዎስ ጋር ሆነው አንድ የሶርያ ተወላጅ ነጋዴ በሐሰት ጳጳሱ እኔ ነኝ እያለ ብዙ ሰዎችን በማሳሳቱ አስረው ወደአገሩ አባረሩት።
- ፲፯፻፷፪ዓ/ም - የስኮትላንድ ተወላጁ ሐዋጼ አህጉር (explorer) ጄምስ ብሩስ በዕለተ ሐሙስ ጎንደር ገባ። እዚሁም እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፯፻፷፬ ዓ/ም ድረስ ተቀመጠ።
- ፲፰፻፹፫ዓ/ም - ታላቁ ደራሲና ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ክቡር ራስ ቢትወደድ መኰንን እንዳልካቸው በሸዋ ግዛት ተጉለት፣ አዲስጌ ላይ ተወለዱ።
የካቲት ፲፩
- ፲፫፻፳፬ዓ/ም - ቀዳማዊ አጼ አምደ ጽዮን በደቡብ ኢትዮጵያ እስላማዊ ግዛቶችን ለማስገበር ዘመቱ።
- ፲፱፻፱ዓ/ም - ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ለራስ ወልደ ጊዮርጊስአቦዬ ዘውድ ጭነውላቸው ንጉሠ ዘቤጌምድርና ስሜን አድርገው ሾሟቸው።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት የመምህራን አድማ ተደረገ። ከዚህም ጋር አብሮ የአዲስ አበባ ታክሲ ነጅዎች አድማ አደረጉ። የታክሲ ነጅዎቹ አድማ ለስድስት ቀናት ቆየ።
- ፲፱፻፷፯ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥትን መስከረም ፪ ቀን የገለበጠውን፣ የኅብረተ ሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር (ደርግ) ለመገርሰስ፣ በቀድሞ አጠራሩ ተጋድሎ ሓርነት ሕዝብ ትግራይ (ተሓሕት"፣ በኋላም ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ተመሠረተ፤ በምዕራባዊ ትግራይ ደደቢት በተባለ ሥፍራም የትጥቅ ትግሉን ጀመረ።
- ፲፱፻፸፰ዓ/ም - የኢትዮጵያ ደራስያን አንድነት ማኅበር (ኢደአማ) ስሙን ወደ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር (ኢደማ) የለወጠበት ዕለት።
የካቲት ፲፪
- ፲፱፻፳፱ዓ/ም - ለኢጣሊያ ንጉሣዊ ቤተሰብ አንድ ልዑል በመወለዱ ምክንያት በጄነራል ግራዚያኒ ትዕዛዝ በቀድሞው የገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቅጽር ግቢ ከተሰበሰቡት የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፤ ለፋሺስቶቹ ያደሩ ከሀዲ ባንዳዎችና መኳንንት፤ የፋሺስት ባለ ሥልጣናት ወታደሮች በተሰበሰቡበት መኻል፣ አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም የእጅ ቦምብ ወርውረው አደጋ ሲጥሉ ግራዚያኒን ጨምሮ ብዙ ሰዎች ተጎድተዋል። ይኸንን ድርጊት በመበቀል ሰበብ እዚያው ግቢ ውስጥ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ተጨፈጨፉ፤ ቀጥሎም የተማሩ ወጣቶች፣ የጦር መኮንኖችና ካህናት፣ የደብረ ሊባኖስ መነኮሳት በሙሉ እየተለቀሙ ተጨፈጨፉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በቤት ውስጥ እያስገቡ ከውጭ ቆልፈው ቤንዚን እያርከፈከፉ አቃጠሉአቸው። በአካፋ፣ በዶማ፣ በመጥረቢያ በተገኙበት ኢትዮጵያውያንን እየቆራረጡ የደም ጎርፍ አወረዱ። ፋሽስቶች የአዲስ አበባንና የአካባቢውን ሕዝብ በጅምላ ጨፈጨፉት። በሶስት ቀናት ፴ሺህ ሕዝብ መስዋዕትነት ተቀበለ።
- ፲፱፻፸፩ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኢቲ-ኤ-ኤፍ ደብልዩ (ET-AFW) ዲሲ ፫ (Douglas C-47B-10-DK፤ በደቡብ-ምዕራብ ኤርትራ በምትገኘው ባረንቱ ላይ በቦምብ ፍንዳታ ተከስክሶ ሲወድቅ አምስቱም ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል። አየር ዠበቡም ከጥቅም ውጭ ሆኗል።
የካቲት ፲፫
- ፲፭፻፴፭ዓ/ም - በዕለተ ረቡዕ አህመድ ግራኝ ወገራ ላይ የንጉሥ ገላውዴዎስን ሠራዊት ገጥሞ በቡርቱጋል ነፍጥ ተመትቶ አህመድ ግራኝ ሲሞት የተረፈው ሠራዊቱ ተሸንፎ ኮበለለ።
- ፲፱፻፴ዓ/ም - በአጋምሳ ላይ ኢትዮጵያውያን አርበኞች ከፋሺስት ኢጣሊያ ጋር ውጊያ ገጠሙ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - በኢትዮጵያ በፈነዳው አብዮት፣ የወጥቶ-እብስ ሠራተኞት የሦስት ቀን አድማቸውን ጀመሩ። በአዲስ አበባ በየቀበሌው እና በየመንገዱ የሚካሄደው ሽብር ቀጥሎ ዋለ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ከቻይና ሕዝባዊ መንግሥት ልዑካን ጋር አዲስ አበባ ላይ የዕርዳታ ስምምነት ተፈራረመ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - የአፍሪቃ፤ የካሪቢያን እና የሰላማዊ ውቅያኖስ አገሮች የንግድ ሚኒስቴሮች ከአውሮፓ የ ኤኮኖሚክ ኅብረት ጋር የንግድ ግንኙነትን ለማጠንከር አዲስ አበባ ላይ ስብሰባቸውን ጀመሩ።
- ፲፯፻፰ዓ/ም - ንጉሥ ዓፄ ዮስጦስ አርፈው እራሳቸው ባሠሩት በጎንደርልደታ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። በህመም ምክንያት ሞቱ ቢባልም፣ በነፍሰ ገዳይ እጅ ታንቀው እንደሞቱ በሰፊው ይታመናል።
- ፲፱፻፶፯ዓ/ም - በአሜሪካ ለጥቁር አሜሪካውያን ሰብአዊ መብት በመታግል የሚታወቀው ማልከም X በኒው ዮርክ ከተማ ላይ በጥይት ተደብድቦ ሞተ።
- ፲፱፻፷፭ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሻንግሃይ፣ ቻይና የበረራ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።[1]
- ፲፱፻፷፭ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በእንግሊዝ አገር ሕክምና ላይ የነበሩትን አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰንን ለመጠየቅ ለአራት ቀን ቆይታ ሎንዶን ገቡ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - በኢትዮጵያ የፈነዳው አብዮት እየተፋፋመ የአዲስ አበባ ከተማ ተሸብሮ ዋለ።
- ፲፱፻፳፱ዓ/ም - ራስ ደስታ ዳምጠውቡታጅራ አካባቢ ላይ በትግራይ ተወላጁ በደጃዝማች ተክሉ መሸሻ ተይዘው በፋሺስት ኢጣልያ እጅ ወደቁ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት ፍንዳታ የተፋፋመውን ሽብር ለመቆጣጠር በተወሰደው እርምጃ፣ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ወታደሮችን በአዲስ አበባ ከተማ ቀበሌዎችና ‘ቁልፍ’ ቦታዎች ለጥበቃ አሰማራ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - ፳፱ የቻይና ‘የወዳጅነት’ ልዑካን አዲስ አበባ ገቡ።
- ፲፱፻፸፩ዓ/ም - ኢትዮጵያ ሕገ ወጥ የአውሮፕላን ጠለፋ ለመከላከል በዓለም ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት የጸደቀውን ስምምነት ፈረመች።
- ፲፱፻፳፱ዓ/ም - በግራትዚያኒ የሚመራ የፋሺስት ኢጣልያ ሠራዊት በዝዋይ አካባቢ የጦር አዝማቾቹን የራስ ደስታ ዳምጠውን እና የደጃዝማች በየነ መርድን አርበኞት ድል አደረጉ። ሁለቱም ኢትዮጵያውያን አዝማቾች ሕይወታቸውን በዚህ ዕለት ሰዉ። ኢጣሊያውያኑ ራስ ደስታን ከያዟቸው በኋላ በጥይት ደበደቧቸው፡፡
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም ኢትዮጵያ ላይ በፈነዳው አብዮት አስገዳጅነት የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የሕዝቡን ሸክም ለማቃለል የነዳጅ ዋጋ ቅነሳን የሚያካትት ኤኮኖሚያዊ እርምጃዎችን እንደሚወስድ ይፋ አደረገ።
- ፲፱፻፳፱ዓ/ም - የግራዚያኒ ሠራዊት በአሩሲና በማረቆ ላይ ትልቅ ጦርነት አድርጎ፣ ራስ ደስታ ዳምጠው እና አብረዋቸው የነበሩትን የጦር አለቆች ማርኮ በዚህ ዕለት በፋሺስቶች እጅ ተገደሉ።
- ፲፱፻፷፭ዓ/ም - ቴኔኮ የተባለ የአሜሪካ ኩባንያ በኦጋዴን ግምቱ ፸፮ ቢሊዮን ሜትር ኩብ የሆነ ሰፊ የተፈጥሮ ነዳጅ (ጋዝ) እንዳገኘ አስታወቀ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - ኢትዮጵያ ላይ በፈነዳው አብዮት በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ በልዕልት ፀሐይ ሆስፒታል አካባቢ ተኩስ ተከፈተ። በዚሁ ዕለት የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ለወታደሮች የደሞዝ ጭመራ ለማድረግ መወሰኑን አስታወቀ።
- ፲፭፻፲፱ዓ/ም - በምድረ አዳል (አሁን አፋር (ክልል)) የባሌው መኮንን ዴገልሃን ሠራዊት ከአህመድ ግራኝ ጋር ጦርነት ገጥሞ የዴገልሃን ሠራዊት በሙሉ ተጨፈጨፈ።
- ፲፮፻፺፪ዓ/ም - ንጉሡ አጼ ኢያሱ ከጎንደር ተነስተው ወደ ጉድሩ ዘምተው እስከ ሰኔወር ድረስ ከቆዩ በኋላ ሐምሌ ፭ ቀን ተመልሰው ጎንደር ገቡ።
- ፲፱፻፶፭ዓ/ም - የሉተራውያን ድርጅት በኢትዮጵያ ‘የወንጌል ድምጽ ራዲዮ’ (ብሥራተ ወንጌል ራዲዮ) ጣቢያአገልግሎቱን ጀመረ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት እንቅስቃሴ፣ አስመራ ላይ የተመደበው የጦር ሠራዊት አድማ መታ።
- ፲፱፻፺፰ዓ/ም - ባለቅኔውና ጸሐፌ ተውኔቱ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅንበተወለደ በ፸ ዓመቱ በዚህ ዕለት አረፈ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት እንቅስቃሴ የወታደሩ አመጽ በሐረር፣ ድሬ ዳዋ፣በደብረ ዘይት ዓየር ኃይል እና በምጽዋ የባህር ኃይል ውስጥ ተቀጣጥሎ ተስፋፋ። የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት መላክተኞች ከ፪ኛ ክፍለ ጦር አባላት ጋር ለመደራደር ወደ አስመራ በረሩ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት ፍንዳታ፣ የወታደሩ አመጽ ተስፋፍቶ አዲስ አበባ የሚገኙ የ፬ ኛ ክፍለ ጦር፤ የጦር ሠራዊት፤ ዓየር ኃይል እና የዋና መሥሪያ ቤት ወታደሮች በከተማው ‘ቁልፍ’ ቦታዎችን በቁጥጥራቸው ሥር አዋሉ። ብዙዎችን የአክሊሉ ሀብተ-ወልድን ሚኒስቴሮች አስረው ያዙ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አቶ እንዳልካቸው መኮንንን ለጠቅላይ ሚኒስትርነት እና ጄኔራል አቢይ አበበን የመከላከያ ሚኒስትር አድርገው ሾሙ። በወቅቱ አዲስ አበባ ላይ ሊካሄድ ተዘጋጅቶ የነበረው የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ስብሰባ በረብሻው ምክንያት ተሰረዘ።
- ፲፱፻፶፪ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጎ አድራጎት ድርጅት በአዋጅ ቁጥር ፪፻፷፩/፶፪ መሠረት ፀደቀ። የድርጅቱ ማቋቋሚያ የአደራ መስጫ ሰነድ (ቻርተር) በሐምሌ ፲፭ ቀን ፲፱፻፶፩ ዓ/ም በመንግሥት ማስታወቂያ ቁጥር ፪፻፶፫/፶፩ መሠረት ወጥቶአል። ይህ ድርጅት በጥቅምት ወር ፲፱፻፷፮ ዓ/ም የደርግ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት በአዋጅ እስከወረሰው ድረስ አገልግሏል።
- ፲፱፻፸ዓ/ም - የኢትዮጵያ ሠራዊት በሶማሊያ ወራሪ ሠራዊት ላይ የካራማራ ድል ተቀዳጀ።
- ፲፱፻፺፩ዓ/ም - የኢትዮጵያ ሠራዊት ባድመን ከኤርትራ ሠራዊት አስለቀቀ።
- ፲፯፻፴፫ዓ/ም - የሸዋው መስፍን መርድ አዝማች አብዬ አረፉ። ቀብራቸውም በሐር አምባ ሚካኤል ተከናወነ። ልጃቸው መርድ አዝማች አምኃ ኢየሱስ ተተክተው ምስፍናውን ያዙ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት የ፬ኛ ክፍለ ጦር አስሯቸው የነበሩትን ሚኒስቴሮች ፈትተው ለንጉሠ ነገሥቱ አስረከቡ። በዚሁ ዕለት በአዲስ አበባ ተማሪዎች የሰላማዊ ሰልፍ ሲያካሂዱ፣ የክብር ዘበኛ ሠራዊት ደግሞ አመጻቸውን ጀመሩ።
- ፲፰፻፹፰ዓ/ም - በዳግማዊ ምኒልክ መሪነት የተሰለፈው የኢትዮጵያ ሠራዊት የጣልያንን ወራሪ ኃይል አድዋ ላይ ድል አድርጎ መለሰው።
- ፳፻፬ዓ/ም - የቴአትር ደራሲ፥ ጋዜጠኛና የቀድሞው የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ሊቀ መንበር፣ ማሞ ውድነህ በተወለዱ በ፹፩ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ።
- ፲፱፻፪ዓ/ም - እቴጌ ጣይቱ ብጡል ከሥልጣን ከመውረዳቸው ከሁለት ሣምንት በፊት፣ ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ዕለት ከሰጡት ሹመቶች አንዱ፣ የሐረርጌን ጠቅላይ ገዥነት ለደጃዝማች ተፈሪ መኮንን (በኋላ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ) ነው።
- ፲፱፻፳፯ዓ/ም - የዐቢይ ጾም ቅበላ ዕለት ዓፄ ኃይለ ሥላሴ መምህር ገብረ ጊዮርጊስን (በኋላ አቡነ ባስልዮስ) እጨጌነት ሾሟቸው።
- ፲፱፻፴ዓ/ም - በሳኡዲ አረቢያ የተፈጥሮ የነዳጅ ኀብት ተገኘ።
- ፲፱፻፶፮ዓ/ም - በኬንያ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ አምባሳዶር ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ በረሩ።
- ፲፱፻፲ዓ/ም - የቤጌምድር እና የስሜን ንጉሥ ወልደ ጊዮርጊስ ደብረ ታቦር ላይ አርፈው እዚያው ተቀበሩ።
የካቲት ፳፭
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - የኢትዮጵያ አብዮት ፍንዳታ ሑከት ወደከርቸሌ እስረኞች ተሸጋግሮ በተከሰተው ረብሻ ፴፮ እስረኞች በጥይት ተገደሉ። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በእንዳልካቸው መኮንን አስተዳደር ውስጥ አዲስ የተሾሙት ሚኒስትሮች ፓትርያርኩ አቡነ ቴዎፍሎስ ፊት ቀርበው ቃለ መኀላቸውን ሰጡ።
- ፲፱፻፷፯ዓ/ም - የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) በሀገሪቱ የገጠር መሬት ተወርሶ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ሀብት ነው የሚል አዋጅ አወጣ። አርሶ መኖር የሚችል ማንኛውም ዜጋም እስከ አስር ሄክታር የሚደርስ መሬት እንደሚሰጠውም ታወጀ።
- ፲፱፻፴፰ዓ/ም - ኢትዮጵያዊው የፊልም ባለሙያ አቶ ኃይሌ ገሪማ በጎንደር ከተማ ተወለዱ።
የካቲት ፳፮
- ፲፱፻፷፭ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ በኢትዮጵያእና በሱዳን መንግሥታት መሃል ውይይት ለማድረግ የኢትዮጵያን ልዑካን መርተው ወደካርቱም አመሩ።
- ፲፱፻፷፮ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሕገ መንግሥቱን አጥንቶ የሚያሻሽል ቡድን መሰየማቸውን ይፋ አደረጉ።
- ፲፱፻፵፱ዓ/ም - ጎልድ ኮስት ትባል የነበረችው የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ጋና ተብላ ነጻ ሆነች። (በወቅቱ ከኢትዮጵያና ከላይቤሪያ ውጭ የመጀመሪያዋ ነጻ አገር መሆኗ ነው።)
*****
የካቲት ፳፱
- ፲፱፻፵፱ዓ/ም - ግብጽ የሱዌዝን ቦይ ከቀውሱ በኋላ መልሳ ከፈተችው።
- ፲፱፻፷፭ዓ/ም - በወለጋ ጠቅላይ ግዛት የቅርፀ ምድር ጥናት ለማካሄድ የሚያስችል የቴክኒክ ስምምነት በኢትዮጵያ እና በጃፓን መሀል ተፈረመ።
- ፲፰፻፹፩ዓ/ም - በሱዳን ግዛት ውስጥ ባለችው ገላባት ላይ በዓፄ ዮሐንስ ፬ኛ የሚመራው የኢትዮጵያ ሠራዊት እና የሱዳን 'ማህዲ' ሠራዊቶች በዚህ ዕለትጦርነት ገጥመው፣ ኢትዮጵያውያኖቹ በማሸነፍ ላይ ሳሉ ንጉሠ ነገሥቱ፣ መጀመሪያ እጃቸው ላይ፤ ቀጥሎም ደረታቸውን በጥይት ስለተመቱ የኢትዮጵያው ሠራዊት ከሥፍራው በማፈግፈግ ሲለቅ ድሉ የ'ማህዲዎቹ' ኾነ። ንጉሠ ነገሥቱም ማታውኑ አረፉ።
- ፲፰፻፹፰ዓ/ም - ኢጣልያም በአድዋ ጦርነት ድል ከተመታች በኋላ በዚሁ ምክንያት ጠቅላይ ሚኒስትሯ ፍራንቼስኮ ክሪስፒ ሥልጣኑን ለቀቀ።
- ፲፱፻፶፪ዓ/ም - የሶቪዬት ሕብረት ፩ ሺህ ተማሪዎችን የሚያስተናገድ የቴክኒክ ትምህርት ቤት (የአሁኑ ባህር ዳር ዩኒቨርስቲ) ባህር ዳር ላይ እንደምትሠራ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት አስታወቀ።
ምንጭ https://am.wikipedia.org/wiki/