አድራሻዬ ይኸውና !
ተመቃብሬም ዘንድ አትድረሱ
ነፍሴ ታውቃለች የለሁም በሱ
በገጾች መካከል መጽሐፍ ገልጣችሁ
አትሮንስ ዘርግታችሁ፣ መዛግብት አገላብጣችሁ
ሰነድ መርምራችሁ ፈልጉኝ ታገኙኛላችሁ።
ከሰዎች አንደበት ላይ ንቅሳት ሆኜያለሁና
እኔም ላገሬ ውለታዋን ከፍያለሁና
አሮጌው ተማሪ ቤቴ እኔን ፍለጋ አትሒዱ
ተአሮጌው ቤቴ እንዳታንጎዳጉዱ
ምሥጢሬ ታደባባይ ወጥቷል ጉዱ
ታውቁኝ ተነበረ ቦታም አትፈልጉኝ
ዛሬ ደከመኝ መሰለኝ ሌላ ገደብ አሰኘኝ
ሰው ነኝና ድንገት ፥ ደከመኝ መሰለኝ
እና ፥ እና ዛሬ ፥ ዛሬ እና
በሰዎች ልብ ውስጥ እነሆ ተኝቼያለሁና
የፈለገኝ ይምጣ አድራሻዬ ይኸውና !
መታሰቢያነቱ ለኢንጀነር ስመኘው በቀለ የሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ በዕለተ ዕርገታቸው ሐምሌ 19 ፥ 2010
ብሩክ በየነ
መነሻ ሐሳብ
“Do not go to my grave.
Mary knows, I am not there.
Look for me in between pages
and on people’s lips.
Do not go to my old school.
Do not go to my old house —
I am not in any of those places.
Look for me in your hearts
and greet me there.”
― Kamand Kojouri
ተመቃብሬም ዘንድ አትድረሱ
ነፍሴ ታውቃለች የለሁም በሱ
በገጾች መካከል መጽሐፍ ገልጣችሁ
አትሮንስ ዘርግታችሁ፣ መዛግብት አገላብጣችሁ
ሰነድ መርምራችሁ ፈልጉኝ ታገኙኛላችሁ።
ከሰዎች አንደበት ላይ ንቅሳት ሆኜያለሁና
እኔም ላገሬ ውለታዋን ከፍያለሁና
አሮጌው ተማሪ ቤቴ እኔን ፍለጋ አትሒዱ
ተአሮጌው ቤቴ እንዳታንጎዳጉዱ
ምሥጢሬ ታደባባይ ወጥቷል ጉዱ
ታውቁኝ ተነበረ ቦታም አትፈልጉኝ
ዛሬ ደከመኝ መሰለኝ ሌላ ገደብ አሰኘኝ
ሰው ነኝና ድንገት ፥ ደከመኝ መሰለኝ
እና ፥ እና ዛሬ ፥ ዛሬ እና
በሰዎች ልብ ውስጥ እነሆ ተኝቼያለሁና
የፈለገኝ ይምጣ አድራሻዬ ይኸውና !
መታሰቢያነቱ ለኢንጀነር ስመኘው በቀለ የሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ በዕለተ ዕርገታቸው ሐምሌ 19 ፥ 2010
ብሩክ በየነ
መነሻ ሐሳብ
“Do not go to my grave.
Mary knows, I am not there.
Look for me in between pages
and on people’s lips.
Do not go to my old school.
Do not go to my old house —
I am not in any of those places.
Look for me in your hearts
and greet me there.”
― Kamand Kojouri
No comments:
Post a Comment