Sunday, August 6, 2017

ሰው ሆይ ስማ!

ሰው ሆይ ስማ! መቼም ስለማትሰማ
ሰው ሆይ ስማ! ጆሮህ ስለማይረባ
ሰው ሆይ አትስማ! አሁን ስለምትሰማ
የሚያገባህን ትተህ በማያገባህ ስትገባ
መታሰቢየነቱ ለአባባ ተስፋዬ ሐምሌ 30, 2017 ያው ወደ ኋላ አልቀርም

Friday, August 4, 2017

ጠጡ






ጠጡ!

ቅዱስ ሆሄያት . . . በፊደል ገበታ መባቻ ሠመሩ




ለሰው ልጅ ሁሉ. . . ጠቃሚ አግባቢ ቃል ሠሩ


. . . ጠ-ጡ !
. . . ጠ-ጡ !

 . . . ጠ-ጡ!


ታለም ስትመጡ ጠጡ ሽርት ውሀ

ባለም ስትኖሩ ጠጡ የግዜር ውሀ

ሻይ፣ ቡና፣ አረቂ፣ ሌላም ብዙ ብዙ

ጠጡ ጨልጡት ዋንጫውን ያዙ

ግን አደራ የራሳችሁን ብቻ ጠጡ

መዘዝ አለው የሰው አትቀላውጡ

መርዝ፣ ደም፣ ጥይት እንዳትጠጡ

ጽዋችሁን ብቻ ጠ-ጡ!

 



የካቲት ፳፪፣ ፳፻፲፰


Albert Camus

አንድና አንድ ብቻ ያልተመለሰ ከባድ የሥነ አስተሳሰብ ጥያቄ አለ፦ እሱም ራስን የማጥፋት ጉዳይ ነው። ሕይወትን መኖር ወይም አለመኖር ልክ ነው ወይም አይደለም ማለት መሠረታዊውን የሥነ አስተሳሰብ ያልተመለሰ ጥያቄ ከመመለስ ጋር ይስተካከላል። ---- አልቤር ካሙ "የሲሲፈስ ምሥጢር" (1942)