Brook Beyene
Sunday, August 6, 2017
ሰው ሆይ ስማ!
ሰው ሆይ ስማ! መቼም ስለማትሰማ
ሰው ሆይ ስማ! ጆሮህ ስለማይረባ
ሰው ሆይ አትስማ! አሁን ስለምትሰማ
የሚያገባህን ትተህ በማያገባህ ስትገባ
መታሰቢየነቱ ለአባባ ተስፋዬ ሐምሌ 30, 2017 ያው ወደ ኋላ አልቀርም
Friday, August 4, 2017
ጠጡ
ጠጡ!
ቅዱስ ሆሄያት . . . በፊደል ገበታ መባቻ ሠመሩ
ለሰው ልጅ ሁሉ. . . ጠቃሚ አግባቢ ቃል ሠሩ
. . . ጠ-ጡ !
. . . ጠ-ጡ !
. . . ጠ-ጡ!
ታለም ስትመጡ ጠጡ ሽርት ውሀ
ባለም ስትኖሩ ጠጡ የግዜር ውሀ
ሻይ፣ ቡና፣ አረቂ፣ ሌላም ብዙ ብዙ
ጠጡ ጨልጡት ዋንጫውን ያዙ
ግን አደራ የራሳችሁን ብቻ ጠጡ
መዘዝ አለው የሰው አትቀላውጡ
መርዝ፣ ደም፣ ጥይት እንዳትጠጡ
ጽዋችሁን ብቻ ጠ-ጡ!
የካቲት ፳፪፣
፳፻፲፰
Albert Camus
አንድና አንድ ብቻ ያልተመለሰ ከባድ የሥነ አስተሳሰብ ጥያቄ አለ፦ እሱም ራስን የማጥፋት ጉዳይ ነው። ሕይወትን መኖር ወይም አለመኖር ልክ ነው ወይም አይደለም ማለት መሠረታዊውን የሥነ አስተሳሰብ ያልተመለሰ ጥያቄ ከመመለስ ጋር ይስተካከላል። ---- አልቤር ካሙ "የሲሲፈስ ምሥጢር" (1942)
Newer Posts
Older Posts
Home
Subscribe to:
Posts (Atom)